መደበኛ ያልሆነ

በአዲስ አበባ ለሚገኙ መምህራን የትምህርት ዝግጅትና ቁጥጥር የሚያደርጉበት እንዲሁም

የትምህርት እቅድ የሚያወጡበት ታብሌት ሊሰጥ ነው።ለዚህ የሚረዱ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ስራዎች እየተከናወኑም ይገኛሉ።

ታብሌቶቹ በሳተላይት የሚገናኙ ሲሆን መረጃዎችን ወደ ማእከል የሚልኩበት መተግበሪያዎችን
ያካተተም ይሆናል።

ከታብሌቶቹ በተጨማሪም የከተማ አስተዳደሩ ዓርማ ያረፈበት ቦርሳ እና ደረጃውን የጠበቀ ገዋን ለለመምህራን የሚያቀርብ ይሆናል።

በመምህራን የሚነሱ የተለያዩ ጥያቄዎችን ለመመለስም የከተማ አስተዳደሩ ትኩረት ተሰጥቶ
እየተሰራ እንደሚገኝ ከከንቲባ ፅ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *