ድጋፍ የተደረገው የህክምና ቁሳቀስ ሙሉ በሙሉ ለጤና ባለሙያዎች የሚሰጥ ሲሆን ፤
የፊት መሸፈኛ ጭንብል ፣ የሙቀት መለኪያ መሣሪያና የህክምና አልባሳትን የሚያካትት
ነው።
የኢትዮጵያ የመድኃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ የህክምና ቁሳቁሶቹን ለየክልሎች የሚያከፋፍል መሆኑም ተገልጿል።
ድርጅቱ ድጋፉን ያደረገው በራሱና በእንግሊዝ መንግሥት እርዳታ መሆኑ ተጠቁሟል።
በኢትዮጵያ የዩኒሴፍ ተወካይ አዴል ኮድር ድጋፉን ለጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ
ማስረከባቸውን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል።