በሳዑዲ ዓረቢያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በሪያድ ግዛት ውስጥ በምትገኘው ደዋድሚ ከተማ ውስጥ በአንድ ቤት ውስጥ አምስት ኢትዮጵያውያን ታግተው እንደነበር በፌስ ቡክ ገጹ አስታወቋል። ከታጋቾቹ ውስጥ አንዱ ወንድ ሲሆን አራቱ ሴቶች መሆናቸውንም ገልጿል።
አጋቾቹ ወደ ታጋች ቤተሰቦች በማስደወል በነፍስ ወከፍ 10 ሺህ የሳዑዲ ሪያል እንዲከፍሉ እና ከዚያ በኋላ እንደሚለቋቸው አሳውቀዋቸዋልም ነው ያለው።
ይህን የማያደርጉ ከሆነም ቅጣቱ ሞት ነው በማለት እንደዛቱባቸው ከታጋች ቤተሰቦች ማወቅ መቻሉን ጠቅሷል።
የተጠየቁትን ገንዘብ የመክፈል አቅም ያልነበራቸው ዜጎችም በአንድ ቤት ተዘግቶባቸው ለብዙ ጊዜያት እንደቆዩም ነው የገለጸው።