
በግብጽ መዲና ካይሮ አል ሀራም በተባለ አዉራጃ ግንባተዉ እየተከናወነ የሚገኘዉ መንገድ ከመኖሪያ አፓርታማ ቤቶች ጋር በ50 ሴ.ሜትር ርቀት ላይ ብቻ መሆኑ ተከትሎ ዉዝግብ አስነስቷል፡፡በመንገዱ ምንክንያት ኑሮቸዉ ለሚስተጓጎል ግብጻዉያን መንግስት ቢያንስ 250 ሚሊየን የግብጽ ፓዉንድ ሊከፈላቸዉ እንደሚገባ የግንባታ ማዕከላዊ ኤጀንሲ ሀላፊ ናስር ተናግረዋል፡፡
የፍጥነት መንገዱ ከመኖሪያ ቤቶቹ እጅግ በጣም የቀረበ መሆኑን ተከትሎ ለኑሮ አስጊ መሆኑ እየተነገረ ይገኛል፡፡ከዚህ በተጨማሪ ከመንገዱ ንድፍ አንስቶ ስህተት እንደነበረበት እየተነገረ ነዉ፡፡
ስምኦን ደረጄ