
ለ20 አመታት በሆድዋ ላይ የማያቋርጥ ህመም ስታሰቃይ የኖረችው ባንግላዲሽያዊት ሴት በቀዶ ህክምና ወቅት ሰውነቷ ውስጥ የተረሳ መቀስ ተገኝቷል፡፡የ55 ዓመቷ ባቸና ኻቱን በ2002 በቹአዳንጋ በሚገኝ ክሊኒክ የሐሞት ጠጠርን የማስወገድ ቀዶ ጥገና ከተደረገላት ጊዜ ጀምሮ የማያቋርጥ የሆድ ህመም ይዟት ነበር። ከህክምናው ሁለት ቀናት በኃላ ሆዴ ውስጥ ህመም ይሰማኛል ስትል ወደ ክሊኒኩ ትመለሳለች፡፡
የቀዶ ጥገና ህክምናዉን የመሩት ሃኪም ስጋቷን ውድቅ በማድረግ ህመሙ የተለመደ እንደሆነ እና መጨነቅ እንደሌለባት ቢገልጹላትም ይህ ግን ስህተት ነበር፡፡የሆድ ህመሟ ተባብሶ በመቀጠሉ ከአንዱ ዶክተር ወደ ሌላ ሐኪም በመሄድ ህክምናዋን ለመከታተል ብትሞክርም የሚታይባትን የህመም ምልክት ለመቅረፍ በሐኪሞች መድኃኒት ሲታዘዝላት ቆይታለች፡፡
ከቅርብ ቀናት ወዲህ የሆድ ህመሟ ለመቋቋም የሚቸግር አይነት መሆኑን ተከትሎ በአንድ በዶክተር ምክር በተደረገላት የኤክስሬይ ምርመራ ከ20 አመታት በፊት በሀሞት ከረጢት ቀዶ ጥገና ህክምና የተረሳው መቀስ ተገኝቷል፡፡በተደረገላት ህክምና መቀሱን ማዉጣት የተቻለ ሲሆን በመልካም ጤንነት ላይ እንደምትገኝ ተነግሯል፡፡
በስምኦን ደረጄ