መደበኛ ያልሆነ

ጥር 9፤2014-በቻይና የወሊድ መጠን ዝቅተኛ ሆኖ ተመዘገበ

በቻይና የወሊድ መጠን በከፍተኛ ደረጃ መቀነስ እየተመዘገበበት የሚገኝ ሲሆን የብሄራዊ ስታቲስቲክስ ቢሮ በዛሬዉ እለት ባወጣዉ መረጃ በ2021 ዓመት የወሊድ ምጣኔ ከ1,000 ሰዎች ወደ 7.52 ዝቅ ብሏል፡፡ ባለፈው አመት ቤጂንግ ጥንዶች እስከ ሶስት ልጆች እንዲወልዱ መፍቀዷ የወሊድ ምጣኔ የጀመረውን የቁልቁለት አዝማሚያ የሚያሳይ ሆኗል፡፡

ቻይና በ2016 ለአስርት አመታት የቆየዉን የአንድ ልጅ መውለድ ፖሊሲ በመሰረዝ የህዝብ ቁጥር ለመጨመር ብታቅድም በርካታ ጥንዶች በከተማ ዉስጥ ባለዉ የኑሮ ውድነት የተነሳ ልጆችን የመውለድ ፍላጎት እያሳዩ አይገኝም፡፡ የስታቲስቲክስ ቢሮ መረጃ እንደሚያሳየዉ ከሆነ ከ1949 ጀምሮ የወሊድ ምጣኔው ዝቅተኛ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

የፒንፖይንት ንብረት አስተዳደር ዋና ኢኮኖሚስት ዡዌይ ዣንግ “የስነሕዝብ ፈተና በደንብ ይታወቃል ነገር ግን የህዝብ የእርጅና ፍጥነት ከተጠበቀው በላይ ሆኗል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡እ.ኤ.አ በ2021 በቻይና 10.62 ሚሊዮን ህጻናት እንደተወለዱ መረጃው ቢያሳይም በ2020 ከተወለዱት 12 ሚሊዮን ህጻናት ጋር ሲነጻጸር እንኳን ቅናሽ አሳይቷል፡፡

በስምኦን ደረጄ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *