መደበኛ ያልሆነ

ጥር 9፤2014-በአዲስ አበባ ባለፉት ስድስት ወራት 29 ዳቦ ቤቶች ግራም ቀነሰው ሲሸጡ በመገኘታቸው እርምጃ ተወስዶባቸዋል

በአዲስ አበባ ከተማ ከ2800 በላይ ዳቦ ቤቶች የሚገኙ ሲሆን ከመንግስት ድጎማ ውጪ ሆነው ራሳቸው የስንዴ ግዢ በመፈጸም ዳቦን ጋጋረው እያቀረቡ ይገኛል።ሸገር ዳቦ በመንግስት በሚደረግለት ድጋፍ ለህብረተሰቡ ዳቦን በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ ነው።

ዳቦ ቤቶች ስንዴን በራሳቸው ወጪ እያቀረቡ በመሆኑ የዳቦውን መጠን የመወሰን መብት ቢኖራቸውም የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ዳቦ ቤቶቹ ባሳወቁት እና በለጠፉት የግራም መጠን ዳቦ እያቀረቡ መሆናቸውን ያጣራል ያሉት በቢሮው የኮሚኒኬሽ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ሚኤሶ ናቸው።በዚህ መሰረት ባለፉት ስድስት ወራት በስነ ልክ ህግ መሰረት ህጉን ተላልፈው የተገኙ 29 ዳቦ ቤቶች ላይ እርምጃ መወሰዱን አቶ ዳንኤል በተለይ ለብሰራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

እርምጃ ከተወሰደባቸው 29 ዳቦ ቤቶች መካከል ሰባቱ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ሲሰጣቸው የተቀሩት ላይ ደግሞ አስተዳዳራዊ እርምጃ ተወስዶባቸዋል፡፡ በቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው አማካኝነት የተጀመረው የዳቦ ፋብሪካ በሂደት ላይ የሚገኝ ሲሆን የግብአት እና የአቅርቦት የሙከራ ስራ ላይ ይገኛል።

ሸገር ዳቦ እያቀረበበት ያለው የዋጋ ተመን ከገበያው አንፃር የማያዋጣ እንዲሁም የስንዴ እጥረት ችግር አጋጥሞት የነበረ ቢሆንም ይህንን ታሳቢ በማድረግ የዋጋው ማስተካከያ እና መንግስት ለማህበረሰቡ ከሚያቀርበው 165 ሺህ ኩንታል ዱቄት ውስጥ 60 ሺህ ኩንታሉን ለሸገር ዳቦ በመስጠት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርብ እየተደረገ ይገኛል ሲሉ አቶ ዳንኤል ጨምረው ለብሰራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

በቤተልሄም እሸቱ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *