መደበኛ ያልሆነ

ጥር 9፤2014-የዓለማችን 10 ሀብታም ሰዎች ሀብት በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት በእጥፍ ጨምሯል ተባለ

ወረርሽኙ የዓለማችንን ሀብታሞች እጅግ ያበለፀገ ቢሆንም በዓለም ዙሪያ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች በድህነት እንዲኖሩ አድርጓል ሲል ኦክስፋም በጎ አድራጎት ድርጅት ገልጿል።ይህዉ ወረርሽኝ በየቀኑ ከ21,000 በላይ ሰዎች ሞት ምክንያት ስለመሆኑ እና እኩልነትን ማስፈን ተገቢ መሆኑን ኢክስፋም በዛሬዉ እለት ባወጣዉ ሪፖርት አስታዉቋል።

የዓለማችን 10 በጣም ሀብታም ሰዎች ከመጋቢት 2020 ጀምሮ የጋራ ሀብታቸው በእጥፍ መጨመሩን ኦክስፋም በዳቮስ በተካሄደው የዓለም ኢኮኖሚክ ፎረም ስብሰባ መጀመሪያ ላይ ስለ ዓለም አቀፍ እኩልነት ባወጣዉ ሪፖርት ላይ አመላክቷል፡፡

የፎርብስ መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የዓለማችን 10 ሀብታም ሰዎች የሚባሉት የቴስላ ባለቤት ኢሎን ማስክ፣የአማዞን ባለቤት ጄፍ ቤዞስ፣ በርናርድ አርኖት እና ቤተሰቡ፣ ቢል ጌትስ፣ ላሪ ኤሊሰን፣ ላሪ ፔጅ፣ ሰርጌ ብሪን፣ የፌስቡኩ ማርክ ዙከርበርግ፣ ስቲቭ ቦልመር እና ዋረን ቡፌት ናቸው።

በአጠቃላይ ሀብታቸው ከ 700 ቢሊዮን ዶላር ወደ 1.5 ትሪሊዮን ዶላር ሲጨምር በመካከላቸው ግን ከፍተኛ ልዩነት አለ፡፡ ለአብነትም የማስክ ሀብት ከ1,000 በመቶኛ በላይ የጨመረ ሲሆን የቢል ጌትስ የሀብት መጠን በአንጻሩ በ30 በመቶ ከፍ ብሏል፡፡

በስምኦን ደረጄ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *