መደበኛ ያልሆነ

ነሐሴ 24፤2015-የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች በጎርፍ ሙላት በመውደቃቸው በአንዳንድ አካባቢዎች የሃይል አቅርቦት ተቋረጠ

የአቃቂ ወንዝ በድንገተኛ ጎርፍ መሙላቱን ተከትሎ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች በመውደቃቸው በአንዳንድ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት እንዲቋረጥ ምክንያት መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል ።

የሃይል አቅርቦት በገላን ኮንዶሚኒየም በከፊል እና በገላን ኮንዶሚኒየም አካባቢ ልዩ ቦታዉ ጫላ የከብት እርባታ እንዲሁም ልደታ ቤተክርስቲያን አካባቢ  የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጡን በአገልግሎቱ የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አ/ቶ መላኩ ታዬ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል ።

አካባቢውም አስቸጋሪ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን የሃይል አቅርቦቱን ወደ ነበረበት ለመመለስ ባለሙያዎች ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ እንደሚገኝ ተገልጿል ።

በአበረ ስሜነህ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *