መደበኛ ያልሆነ

መስከረም 7፤2016-የ5 ሺህ ሜትር የዓለም ሪከርድ ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰ

በዩጂን በተደረገ የዳይመንድ ሊግ  የፍፃሜ ውድድር አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ የ5,000ሜ የዓለም ሪከርድን በመስበር አሸንፋለች።

14:00.21 በሆነ ሰዓት የገባችው ጉዳፍ ፀጋይ የዓለም ሪከርዱን ከኬንያዊቷ ፌዝ ኪፕዬጎን በመንጠቅ ሪከርዱን የግሏ ማድረግ ችላለች።

” ትኩረቴ የነበረው የዓለም ሪከርዱን መስበር ነበር ”  ያለችው ጉዳፍ በተመዘገበው ድል በጣም ደስተኛ መሆኗን እና በቀጣይ ከአስራ አራት ደቂቃ በታች ለመግባት እንደምትጥር ከድሉ በኋላ ተናግራለች።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *