መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 21፤2016 – በሀላባ ዞን በበሬ ስርቆት የተከሰሰው ግለሰብ 6 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን በሀላባ ቁሊቶ ከተማ በሬ ሰርቆት ሲንቀሳቀስ እጅ ከፈን የተያያዘ ተከሳሽ 6 ዓመት ፅኑ እስራት መቀጣቱ ተነግሯል ።

ተከሳሽ ሀብታሙ ማቲዮስ ተገቢ ያልሆነ ብልጽግና ለራሱ ለማግኘት በማሰብ ለጊዜው በህግ ቁጥጥር ስር ካልዋለው አቢቲ ግዛው ጋር ህዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም በግምት ከምሽቱ 7:30 በሚሆንበት ጊዜ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ዛላ ፍሬ ቀበሌ የግል ተበዳይ አ /ቶ ሙንዲኖ ኢብራሂም የሆነውን ግምቱ 50 ሺህ ብር የሚያወጣውን በሬ ግንብ አጥር ዘሎ በመግባት እንደሰረቀ ተገልጿል ።

በሬውን ከሰረቀ በኋላ ሲንቀሳቀስ እጅ ከፍንጅ በፖሊስ የተያዘ ሲሆን ተከሳሽ በፈፀመው ከባድ ስርቆት ወንጀል ዓቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል ። ጉዳዩ የተመለከተው የሀላባ ቁሊቶ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ተከሳሽን ጥፋተኛ ሲል በ6 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ።

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 21፤2016 – በማዳጋስካር ምርጭ ፕሬዝዳንት ራጆኦሊና በድጋሚ አሸነፉ

የማዳጋስካር ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤት ከሁለት ሳምንት በፊት የተካሄደውን አወዛጋቢ ምርጫ ተከትሎ ፕሬዚዳንት አንድሪ ራጆኤሊና በድጋሚ መመረጣቸውን አረጋግጧል። ፍርድ ቤቱ ራጆኤሊና ከተሰጠው ድምጽ 59 በመቶ የመራጮችንድ ድምፅ በማግኘት ለሶስተኛ ጊዜ መመረጣቸውን አስታውቋል። በምርጫው ተዓማኒነት ላይ ተቃዋሚዎች ያቀረቡትን ቅሬታ ውድቅ አድርጓል።

አብዛኞቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምርጫውን ውድቅ በማድረግ ተቀባይነት የለውም ብለዋል። “አንድሪ ራጆኤሊና የማዳጋስካር ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሆነው በመመረጥ ቃለ መሃላ መፈፀማቸውን የሕገ መንግሥት ፍርድ ቤት ኃላፊ የሆኑት ፍሎሬንት ራኮቶአሪሶአ ለሮይተርስ የዜና ወኪል ተናግረዋል።ከ 13 ፕሬዚዳንታዊ ተፎካካሪዎች አስሩ ካእጩነታቸውን ራሳቸውን አግለው በምርጫው ሳይሳተፉ ቀርተዋል።

በምርጫው ተዓማኒነት ላይ ስጋት በማንሳት ደጋፊዎቻቸው ድምጽ እንዳይሰጡ በመጠየቅ በደሴቲቱ ሀገር ታሪክ ዝቅተኛው የህዝብ ተሳትፎ የተደረገበት ምርጫ በሚልም ተመዝግቧል። በተጨማሪም ራጆኤሊናን ለሶስተኛ ጊዜ ለፕሬዝዳንትነት ለመወዳደር ያቀረቡትን ጥያቄ እና የእጩነቱን ትክክለኛነታቸው የፈረንሣይ ጥምር ዜግነት ያላቸው በመሆኑ ተቃዋሚዎች አውግዘዋል።

የሕገ መንግሥታዊ ፍርድ ቤት አስቀድሞ የራጆኤሊናን በድጋሚ ለሶስተኛ የሥልጣን ዘመን ለመወዳደር ያቀረቡትን ጥያቄ ውድቅ አድርጎ ነበር።የራጆኤሊና ሁለቱ የቅርብ ተቀናቃኞቻቸውን ስቴኒ ራንድሪያናሶሎኒያኮ እና የቀድሞ ፕሬዚደንት ማርክ ራቫሎማናናን በቅደም ተከተል 14% እና 12% ድምጽ አግኝተዋል።

ከምርጫው በፊት ለሳምንታት የዘለቀው ሰላማዊ ሰልፎች እና ከፖሊስ ጋር ግጭት የተፈጠረ ሲሆን ተቃዋሚዎች ራጆኤሊና ኢፍትሃዊ የምርጫ ሁኔታዎችን ፈጥረዋል ሲሉ ከሰዋል።ራጆኤሊና ግን ክሱን ውድቅ አድርገዋል። ዩናይትድ ስቴትስ እና የአውሮፓ ህብረት ፕሬዚዳንቱ እንዲነጋገሩ እና የምርጫ ማሻሻያዎችን እንዲያካሂዱ ዓለም አቀፍ ጥሪዎችን አድርገዋል ።

በሚሊዮን ሙሴ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 21፤2016 –በጋዛ ከሰባት ቀናት የተኩስ እረፍት በኃላ ጦርነት ተቀሰቀሰ

???? ባገረሻው ግጭት ከ70 በላይ ፍልስጤማውያን ተገድለዋል

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በጋዛ ዳግም ጦርነት በመጀመሩ በጣም ተጸጽቻለሁ ብለዋል።

በማህበራዊ ድረ-ገፅ ላይ ባሰፈሩት መግለጫ መሰረት አሁንም የተኩስ አቁሙ ይመለሳል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ሲሉ ተደምጠዋል። ወደ ጦርነቱ መመለስ እውነተኛ ሰብአዊ የተኩስ አቁም ማድረግ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ብቻ ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል። ጋዛን የሚያስተዳድረው የሃማስ የጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው እስራኤል የጦር ዘመቻዋን ከጀመረች ወዲህ ወደ 6,000 የሚጠጉ ህጻናትን ጨምሮ ከ14,800 በላይ ሰዎች ተገድለዋል ብለዋል።

በጥቅምት 7 ሃማስ በእስራኤል ላይ ጥቃት ሰንዝሮ 1,200 ሰዎችን ሲገድል 240 የሚጠጉ ሰዎችን አግቶ ወደ ግዛቱ መውሰዱ ይታወሳል።ባለፈው ሳምንት ከታጋቾቹ ውስጥ ከ100 በላይ የሚሆኑት የተለቀቁ ሲሆን ፍልስጤማውያን እስረኞችን ከእስራኤላውያን እስር ቤቶች ለማስለቀቅ ተችሏል።በእስራኤል እና በሃማስ መካከል ለሰባት ቀናት የዘለቀው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ያለተጨማሪ ማራዘሚያ ካበቃ በኋላ በጋዛ ጦርነቱ ቀጥሏል።

በመላው ጋዛ ከባድ የተኩስ ልውውጥ እና በርካታ ትላልቅ የአየር ድብደባዎች ታይተዋል እንዲሁም ተሰምተዋል። የእስራኤል ጦር እንዳስታወቀው ሮኬቶች በደቡብ እስራኤል ላይ ከጋዛ ሰርጥ ተተኩሰዋል። በጋዛ ታግተው የነበሩትን ሴት እና ህጻናትን ሙሉ በሙሉ ማስለቀቅ ባለመቻሉ ሃማስን የእስራኤል ጦር ተወቃሽ አድርጓል። እርቁ ከማብቃቱ በፊት ሮኬቶች ወደ እስራኤል ተተኩሰዋልም ብሏል።

ሀማስ በበኩሉ የተኩስ አቁም ስምምነቱን በማፍረስ እስራኤልን በመወንጀል የነዳጅ አቅርቦቶችን ወደ ሰሜን ጋዛ እንዳይደርስ አድርጋለች ብሏል።በጋዛ ሃማስ የሚመራው የጤና ሚኒስቴር ጦርነቱ ካገረሸ በኋላ ባሉት ሰአታት ውስጥ ቢያንስ 70 ሰዎች በአየር ድብደባ መገደላቸውን አስታውቋል ። በደቡባዊው ከተማ ከካን ዮኒስ በስተምስራቅ የሚገኙ ሰዎች በግብፅ ድንበር አቅራቢያ ወደምትገኘው ወደ ራፋህ እንዲሄዱ የሚያስጠነቅቅ በራሪ ወረቀቶች ተበትነዋል።

የእስራኤል የመከላከያ ሰራዊት ጋዛን በመቶዎች በሚቆጠሩ ዞኖች የሚከፋፍል አዲስ ካርታ የሰራ ሲሆን ይህም “ለቀጣዩ የጦርነት ደረጃ ዝግጁነት” ሰላማዊ ዜጎችን ለቀው እንዲወጡ የሚፈልጓቸውን አካባቢዎች ለማስጠንቀቅ ይጠቅማል ተብሏል።በኳታር የተኩስ አቁሙን ለማስቀጠል አስቸጋሪ የተባለው ድርድር እንደቀጠለ ምንጮች ተናግረዋል።

ጦርነቱ እንደገና ከመጀመሩ በፊት የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ለእስራኤል እንደተናገሩት በዚህ ጊዜ ሰላማዊ ዜጎችን በተለየ መንገድ መጠበቅ እስራኤል እንዳለባት ገልፃዋል።በሰሜን ጋዛ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዜጎች ሞት እና የጅምላ መፈናቀል በደቡብም ሊደገም እንደማይገባም አሳስበዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህጻናት ኤጀንሲ እርቁ ካልቀጠለ በቀር ሰብአዊ ጥፋት እንደሚመጣ አስጠንቅቋል። በደቡባዊ ጋዛ በሚገኝ ሆስፒታል የዩኒሴፍ ቃል አቀባይ ሁኔታውን አስፈሪ ሱል ገልጿል።

በስምኦን ደረጄ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 21፤2016 – በኢትዮጽያ በዓመት ከ8 ሺህ በላይ ሰዎች በኤች አይ ቪ እንደሚያዙ ተገለፀ

በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ከ610 ሺ በላይ የሚሆኑ ግለሰቦች ኤች አይ ቪ ኤድስ በደማቸው ውስጥ እንደሚገኝ  እና በዓመት 8,257 ሰዎች ደግሞ  በቫይረሱ እንደሚያዙ የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከል እና ቁጥጥር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ያደታ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን   ተናግረዋል።

በዛሬው እለት የዓለም የኤድስ ቀን የማህበረሰብ መሪነት ለላቀ ኤች አይ ቪን መከላከል በሚል መሪ ቃል በመላው ዓለም ታስቦ ውሏል። በኢትዮጵያ በዓመት ውስጥ በቫይረሱ ምክንያት የሚከሰት ሞት መጠን በ2010 ከነበረበት በ52 በመቶ መቀነስ መቻሉን ብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ከጤና ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያሳያል።

በ2022 በዓለም አቀፍ ደረጃ 39 ሚሊዮን ሰዎች  ኤች አይቪ በደማቸው እንደሚገኝ ከእነዚህም 630,000 የሚሆኑት ህይወታቸውን ማጣታቸው ተነግሯል። 1.3 ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ  አዲስ የሚያዙ ሰዎች ሲሆኑ  ኢትዮጽያን ጨምሮ በመላው ዓለም በተሰራ ጥናት ሴቶች በቫይረሱ  ይበልጥ ተጠቂ  መሆናቸው ተጠቁሟል።

በ2025 ኤች አይ ቪ በደማቸውመገኘቱን የሚያውቁ ሰዎች ውስጥ 95በመቶ የሚሆኑትን የጸረ ኤች አይቪ ህክምና እንዲያገኙ ማድረግ እና ህክምና የጀመሩትን ክትትላቸውን በማስቀጠል በደማቸው ያለውን የቫይረስ መጠን ዝቅ በማድረግ ዙሪያ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራ ተጠቁሟል።የኤች አይቪ ኤድስ ሰርጭት መጠኑ ከክልል ክልል የሚለያይ ሲሆን  ከፍተኛ የስርጭት መጠን የሚታይበት ቀዳሚው ክልል ጋምቤላ ሲሆን  አዲስ አበባ እና ሀረሪ ክልል የሁለተኛ እና ሶስተኛ ቦታዎችን ይዘው ይገኛሉ።

በሌላ በኩል ደግሞ ዝቅተኛ የስርጭት መጠን የሚታይበት ክልል ሶማሌ ክልል መሆኑን አቶ ፍቃዱ ያደታ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

በኤደን ሽመልስ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 19፤2016 -ከሀማስ ጥቃት ወዲህ በዌስት ባንክ ከ3,300 በላይ ፍልስጤማውያን በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ተሰማ

የፍልስጤም እስረኞች ማህበር እና የእስረኞች ጉዳይ ባለስልጣን የእስራኤል ሃይሎች የ12 አመት ህጻን ጨምሮ 35 ፍልስጤማውያንን በዌስት ባንክ ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በቁጥጥር ስር ማዋላቸውን አስታውቀዋል። ከጥቅምት 7 ጀምሮ የተያዙት አጠቃላይ ሰዎች ቁጥር አሁን ላይ ከ3,325 በላይ ደርሷል ሲል ማህበሩ በፌስቡክ ገፁ ላይ ባወጣው የጽሁፍ መግለጫ ገልጿል።

በሌላ በኩል ገለልተኛ ጋዜጠኛ ኦር-ሊ ባሌቭ እንደዘገበው በእየሩሳሌም በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ፊት ለፊት በዛሬው እለት በተካሄደ የተቃውሞ ሰልፍ ኔታንያሁ ስልጣን እንዲለቁ ሰልፈኞች ጠይቀዋል።

ፖሊስ ሰልፈኞችን ድርጊታቸውን ህገወጥ በማለት በቁጥጥር ስር አውሏል።ሃማስ የተኩስ አቁም ስምምነቱ ሊራዘም እንደሚችል የገለፀ ሲሆን በኳታር አዲስ ድርድር እየተካሄደ ይገኛል።እስራኤል በጋዛ የተያዙ ታጋቾች ስም ዝርዝር እንደደረሳት ተናገራለች። በዛሬው እለት ሊለቀቁ እንደሚችልን ይጠበቃል። የተኩስ አቁም ስምምነቱ ስድስተኛው ቀን ይዟል።

በስምኦን ደረጄ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 18፤2016 – በፍሎሪዳ አንዲት ሴት የወንድ ጓደኛዬ ሌላ ሴት ያያል በሚል ሰበብ በእብድ ውሻ መርፌ ዓይኑን በመውጋቷ ተከሰሰች

በፍሎሪዳ ነዋሪ የሆነችው ግለሰብ ሴት ፍቅረኛዋ ሌሎች ሴቶችን እየተመለከተ ነው በማለት በእብድ ውሻ መርፌ ወግታለች ከተባለች በኋላ በቁጥጥር ስር ውላለች።

የ44 ዓመቷ ሳንድራ ጂሜኔዝ በተመለከተ የኦርላንዶ የሚያሚ-ዴድ ፖሊስ ክፍል እንዳስታወቀው ቅዳሜ ከጓደኛዋ ጋር አብረው በሚኖሩበት ቤት ውስጥ ከተፈጠረ ክስተት ጋር በተያያዘ ተከሳለች። በመርፌ ስለተወጋው ሰው የጤና ሪፖርት የፖሊስ መኮንኖች ከሆስፒታል ምላሽ አግኝተዋል።

ተጎጂው ለፖሊስ እንደተናገረው ፍቅረኛው ጂሜኔዝ “ሌሎች ሴቶችን ትመለከታል” በሚል የተነሳውን ክርክር ተከትሎ የውሻችንን የእብድ ውሻ መርፌ በማንሳት የቀኝ ዐይኔን ሽፋኑን ለመውጋት ተጠቅማበታለች ሲል ተናግሯል ።ጂሜኔዝ የስምንት አመት ፍቅረኛዋን ሶፋ ላይ በተኛበት ወቅት ይህንኑ ድርጊት የፈፀመች ሲሆን ከጥቃቱ በኃላ ከቤት በመውጣት መጥፋቷ ተሰምቷል።

ተጎጂው ወደ 911 ደውሎ በፍጥነት ወደ ሆስፒታል ከተወሰደ በኃላ ስለደረሰበት ጥቃት ለፖሊስ መኮንኖች ተናግሯል።ፖሊስ ተከሳሿን ጂሜኔዝ ከቤት ውጭ በቆመው መኪና ውስጥ ተኝታ እንዳገኛት እና በቁጥጥር ስር በማዋል ቃሏን መቀበሉን ገልጿል።

ጂሜኔዝ ስለ ተፈጸመው ጥቃት ፖሊስ ሲጠይቃት የወንድ ጓደኛዋ ጉዳቱ በራስ ላይ ነው ያደረሰ  ስትል ክዳለች።በ 7,500 የአሜሪካን ዶላር ዋስ መለቀቋ ተሰምቷል።

በስምኦን ደረጄ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 18፤2016 – በአሶሳ ከተማ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥይት በመተኮስ ግድያና ከባድ የአካል ላይ ጉዳት ያደረሱት ሁለት የፀጥታ ሃይሎች በእስራት ተቀጡ

በአሶሳ ከተማ አስተዳደር በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥይት በመተኮስ ግድያና ከባድ የአካል ላይ ጉዳት ያደረሱት ሁለት የፀጥታ ሃይሎች በ15 ዓመት ፅኑ እስራት መቀጣታቸውን የአሶሳ ከተማ አስተዳደር የወረዳ ሁለት ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሳጅን እሸቱ ተስፋየ ለብስራት ራዲዮ እና ቴሌቪዥን ገልፀዋል።

1ኛ ተከሳሽ  ወርቁ በላይ ደቢሳ የተባለው ግለሰብ በአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ቀጠና ሁለት ልዩ ቦታው ግብርና ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አከባቢ በዕለተ ቅዳሜ መጋቢት 23 ቀን 2015 ዓ/ም በግምት 4:30 ሰዓት ሲሆን ሠውን ለመግደል  አስቀድሞ በነበረው ሃሳብ በመነሳሳት መንግስት ለስራ ጉዳዩ ባስታጠቀው ባለ ሰደፍ ክላሽንኮቭ መሳሪያ  ሆን ብሎ እና አስቦ ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ሟች አቶ አመንቴ ታሪኩ የተባለው ላይ በመተኮስ በአንድ ጥይት በመምታት ህይወቱ እንዲያልፍ ያደረገ ሲሆን በከባድ የግድያ ወንጀል ተከሷል።

2ኛ ተከሳሽ መኩሪያ ሃምቢሳ ባሮ የተባለው ተከሳሽ በአንደኛ ተከሳሽ ላይ በተገለፀው ጊዜ እና ቦታ ላይ ሠውን ለመግደል  አስቀድሞ በነበረው ሃሳብ በመነሳሳት መንግስት ለስራ ጉዳዩ ባስታጠቀው ባለ ሰደፍ ክላሽንኮቭ መሳሪያ  ሆን ብሎ በጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ የግል ተበዳይ 1ኛ አቶ እስራኤል በንቲ  አና  2ተኛ ተበዳይ አቶ ብሩክ ቤከማ የተባሉትን ግለሠቦች በጥይት በመምታት ከባድ ጉዳት ሲሆን ተከሳሽ በፈፀመው በከባድ የሰው መግደል ሙከራ ወንጀል ተከሷል።

ስለሆነም ሁለቱም ተከሳሾች የወንጀል ድርጊቱን ከፈፀሙ ቡኋላ ከአከባቢው  ለመሠወር ሲሞክሩ ፖሊስ ከህብረተሰቡ እና ከሌሎች የፀጥታ ሃይሎች ጋር  በመቀናጀት ባደረጉት ክትትል በአሶሳ ዞን ሆሞሻ ወረዳ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን እና ክስ የተመሠረተባቸው መሆኑን የፖሊስ የምርመራ መዝገብ ያስረዳል።የአሶሳ  ከተማ አስተዳደር የወረዳ ሁለት መርማሪ ፖሊስ እና ዐቃቤ-ህግ በጋራ በመሆን የምርመራ መዝገቡን በሠው ፣ በተያዘው የሠነድ ማስረጃ እና በህክምና ማስረጃ በማስደገፍ ለአሶሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርበዋል፡፡

ክሱ የደረሰው የአሶሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተጣርቶ የቀረበለትን የምርመራ መዝገቡን ከተመለከተ በኋላ የተከሳሾችን ጥፋተኝነትን በማረጋገጥ የወንጀል ማክበጃ እና ማቅለያ በማነፃፀር በትላንትናዉ እለት ህዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሾች ጥፋተኛ ሁነው በመገኘታቸው እና ተከሳሾችን ያርማል ሌላውን ማህበረሰብ ያስተምራል በማለት እያንዳንዳቸውን በ15 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ መወሰኑን የአሶሳ ከተማ አስተዳደር የወረዳ ሁለት ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሳጅን እሸቱ ተስፋዬ ጨምራ ለብስራት ራዲዮ አና ቴሌቬዥን ተናግረዋል  ።

በበቀለ ጌታሁን

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 18፤2016 – አንድ እስራኤላዊ ከእገታ ሲለቀቅ በምትኩ ሶስት ፍልስጤማዉያን ከእስር እንዲለቀቁ የሚያስችለዉ ስምምነት ለ48 ሰዓታት ተራዘመ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእስራኤልን ወታደራዊ ጥቃት በከፍተኛ ደረጀ ወደደረሰባት ሰሜናዊ ጋዛ በርካታ ቶን እርዳታ ደርሷል ሲል አስታውቋል።

አቅርቦቶቹ ለመመገብ የተዘጋጁ ምግቦችን፣ የመጠጥ ውሃ፣ ድንኳን እና ብርድ ልብስ እንዲሁም መድሃኒቶችን እንደሚያካትት የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኦቻ አስታውቋል። ለኤሌትሪክ ማምረቻ የሚሆን ነዳጅ እና ለስራ ማስኬጃ የሚሆን እና የፍሳሽ ማጣሪያ እንዲሁም የውሃ ማስወገጃ መሳሪያዎች ተልኳል።

ከእስራኤል በኩል በሁለት ማስተላለፉያ መስመሮች የመጠጥ ውሃ በደቡብ ጋዛ ላሉ ሰዎች እየቀረበ ነው ሲል ኦቻ ተናግሯል። በእስራኤል እና በሃማስ መካከል የተካሄደው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ለ48 ሰአታት ለማራዘም ስምምነት ላይ ከተደረሰ በኋላ ዛሬ አምስተኛ ቀኑን ይዟል።

ከጋዛ ለተመለሰ እያንዳንዱ እስራኤላዊ ታጋች ምትክ ሶስት ፍልስጤማውያን ከእስራኤላውያን እስር ቤቶች ይለቀቃሉ።ነገር ግን ሃማስ በጋዛ ሰርጥ ያሉትን ምርኮኞች በሙሉ አልያዝኩም ማለቱ ተጋቾችን ለማስለቀቅ የሚደረገውን ጥረት ሊያወሳስበው ይችላል ተብሏል። የኳታር ከፍተኛ የሃማስ ምንጭ እንደተናገሩት ከሲቪል ታጋቾች መካከል የተወሰኑት በሌሎች ትናንሽ ታጣቂ ቡድኖች ተይዘዋል ብለዋል።

የጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ጽህፈት ቤት ዛሬ ረፋድ ላይ የሚፈቱ እስረኞች ስም ዝርዝር እንደደረሳቸው እና ቤተሰቦቻቸው እንዲያውቁ እየተደረገ ነው ብለዋል። ትናንት ማምሻውን ከእስር ከተፈቱት መካከል ሁለት ሴቶች እና ዘጠኝ ህጻናት እና ታዳጊዎች ሲሆኑ ሁሉም ከአንድ አካባቢ ታፍነው ተወስደዋል።

በዛሬው እለት 10 ታጋቾች እና በነገው እለት ረቡዕ 10 ታጋቾች ይለቀቃሉ ተብሎ ይጠበቃሉ።ነገር ግን እነዚህ ቁጥሮች በእስራኤል ዘንድ አልተረጋገጠሙ
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በጣም አስፈላጊ የሆነውን እርዳታ ወደ ጋዛ ለማድረስ የትግሉ መቆም እንዳገዘው ተነግሯል። ነገር ግን ተጨማሪ የተኩስ አቁም መራዘም እንዲኖር ጠይቋል።

በስምኦን ደረጄ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 18፤2016 – የዩክሬን የስለላ ቢሮ ኃላፊ ሚስታቸው መመረዟ ተሰማ

የዩክሬን የስለላ ሃላፊ ሌተናል ጀነራል ኪሪሎ ቡዳኖቭ ባለቤት በከባድ ሁኔታ መመረዟን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙህን ዘግበዋል። ማሪያና ቡዳኖቫ ለ”ረዥም ጊዜ ህመም” ከተሰማት በኋላ ወደ ሆስፒታል ተወስዳለች ሲል ባቤል የተሰኘ የዜና አውታር የስለላ ባለስልጣናትን ጠቅሶ ዘግቧል። ሌሎች ሁለት የዩክሬን ሚዲያዎች በራሳቸው ምንጮች ላይ ተመስርተው ተመሳሳይ መረጃዎችን አጋርተዋል።

የዩክሬን ወታደራዊ ኃይል በወጡት ዘገባዎች ላይ በይፋ የሰጠው አስተያየት የለም። ከጥቃቱ ጀርባ ሩሲያ እጇ አለበት ተብሎ ይታሰባል።የዩክሬኑ ዩክሬንካ ፕራቫዳ የዜና ድረ-ገጽ እንዳስታወቀው ሌሎች በርካታ የስለላ ባለስልጣናትም ተመርዘዋል ብላል።ሆኖም ጄኔራል ቡዳኖቭ የዚሁ ምረዛ ኢላማ ተደርገው ሊሆን ይችላል የሚሉ አስተያየቶች አልተሰጡም።

በየካቲት 2022 የሞስኮን ሙሉ ወረራ ተከትሎ በዩክሬን የመከላከያ ሚኒስቴር ዋና የመረጃ ዳይሬክቶሬት የሚመሩት ጄኔራሉ፣ ከፍተኛ ወታደራዊ ዘመቻዎችን በማቀድ እና አንዳንድ ጊዜ በሩሲያ ኃይሎች ላይ ለሚወሰዱ እርምጃዎች ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል ተብሎ ስማቸው ይነሳል።

የዜና ድረ-ገጽ ባቤል የጄነራሉ ሚስት መመረዛቸውን በዛሬው እለት ቀድሞ የዘገበ ሲሆን የዩክሬን የስለላ መረጃ ምንጮቹን ጠቅሶ እንዳለው ቡዳኖቫ አሁን ህክምናውን እያጠናቀቀች እንደሆነ እና በዶክተሮች ክትትል እንደሚደረግላት ገልጿል። ስማቸው ያልተጠቀሰው ባለስልጣናት አክለውም ቡዳኖቫ የተመረዙባቸው ንጥረ ነገሮች “በዕለት ተዕለት ኑሮ ወይም በወታደራዊ ስራዎች ውስጥ በምንም መልኩ ጥቅም ላይ አልዋሉም” ብለዋል ።

ምናልባት የተመረዘ ምግብ ተሰጥቷት የነበረ ቢሆንም አሁን ግን የመጀመሪያ ህክምናዋን ካጠናቀቀች በኋላ “የተሻለ ስሜት እየተሰማት ነው” ተብሏል። በተናጥል የዩክሬን ዩኒያን የዜና ወኪል ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው ወይዘሮ ቡዳኖቫ በዩክሬን ውስጥ ህክምና እየተደረገላቸው ነው እንጂ ወደ ውጭ ሀገር አልወጡም ብሏል ። ወይዘሮ ቡዳኖቫ እ.ኤ.አ. በ 1993 በኪዬቭ ከተማ የተወለደች ሲሆን በስነ-ልቦና የማስተርስ ዲግሪዋን ተቀብላለች። ከዛም የኪየቭ ከተማ ከንቲባ አማካሪ ሆና በፖለቲካ ውስጥ ተሳትፋለች።

በስምኦን ደረጄ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 18፤2016 – በኦሮሚያ ክልል በደረሰ በትራፊክ አደጋ የ 20 ሰዎች ህይወት አለፈ

በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን ተልታሌ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ20 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰምቷል።

ከሟቾች በተጨማሪም በአደጋው ምክንያት በ18 ሰዎች ላይ ከባድ እንዲሁም በ14  ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን ብስራት ከዞኑ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያገኘዉ መረጃ ያመላክታል፡፡

አደጋው የደረሰው የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከሚላሚ ከተማ ወደ ዋዩ ሲጓዝ መንገድ ስቶ መገልበጡ መሆኑ ተነግሯል።

በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው በተልታሌና ወላይታ ሆስፒታሎች የህክምና እርዳታ እንዲያገኙ መላካቸውን ጣቢያችን ሰምቷል።