ኢኳዶር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ያወጀች ሲሆን “እጅግ አደገኛ” የአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪ ከከፍተኛ የጸጥታ እስራት ቤት ማምለጡን ተከትሎ ሁከት በተከሰተባት ሀገር ውስጥ በበርካታ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ አለመረጋጋት ተፈጥሯል።ከህዳር ወር ጀምሮ በስልጣን ላይ የሚገኙት ፕሬዝዳንት ዳንኤል ኖቦአ በኢኳዶር ጎዳናዎች እና ማረሚያ ቤቶች ውስጥ ባ ለ60 ቀናት የሚቆይ ወታደራዊ ዘመቻን በማስጀመር ጆሴ አዶልፎ ማሲያስን ፊቶ እንዲታደን ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በየቀኑ ከሰዓት እላፊ ገደብ ጋር እንደሚተገበር ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በተመለከተ ፕሬዝዳንት ኖቦ በኢንስታግራም ላይ በለቀቁት ቪዲዮ አሸባሪዎች ካሏቸዉ የአደንዛዥ እጽ አዘዋዋዋሪዎች ጋር በሚደረገው ውጊያ ተግባራቸውን ለመወጣት “ሁሉንም የፖለቲካ እና የህግ ድጋፍ” ለወታደራዊዉ ኃይል እንደሚሰጣቸው ተናግረዋል።
ፊቶ ከ2011 ጀምሮ በተደራጀ ወንጀል፣ በአደንዛዥ ዕፅ አዘዋዋሪነት እና በግድያ ወንጀል የ34 አመት እስራት ተፈርዶበት ነበር።ከማረሚያ ቤት ሲያመልጥ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን እ.ኤ.አ. በ 2013 ከማረሚያ ቤት አምልጦ ከሶስት ወራት በኋላ እንደገና ተይዟል፡፡በሺዎች የሚቆጠሩ የጸጥታ ሃይሎችን ባሳተፈ ኦፕሬሽን ፊቶ ባለፈው ነሃሴ የፕሬዝዳንት እጩ ፌርናንዶ ቪላቪሴንሲዮ መገደሉን ተከትሎ ከፍተኛ ጥበቃ ወደሚገኝ እስር ቤት ተዘዋውሯል።
በስምኦን ደረጄ