መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 21፤2016 – በሀላባ ዞን በበሬ ስርቆት የተከሰሰው ግለሰብ 6 ዓመት ፅኑ እስራት ተቀጣ

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን በሀላባ ቁሊቶ ከተማ በሬ ሰርቆት ሲንቀሳቀስ እጅ ከፈን የተያያዘ ተከሳሽ 6 ዓመት ፅኑ እስራት መቀጣቱ ተነግሯል ።

ተከሳሽ ሀብታሙ ማቲዮስ ተገቢ ያልሆነ ብልጽግና ለራሱ ለማግኘት በማሰብ ለጊዜው በህግ ቁጥጥር ስር ካልዋለው አቢቲ ግዛው ጋር ህዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም በግምት ከምሽቱ 7:30 በሚሆንበት ጊዜ በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ዛላ ፍሬ ቀበሌ የግል ተበዳይ አ /ቶ ሙንዲኖ ኢብራሂም የሆነውን ግምቱ 50 ሺህ ብር የሚያወጣውን በሬ ግንብ አጥር ዘሎ በመግባት እንደሰረቀ ተገልጿል ።

በሬውን ከሰረቀ በኋላ ሲንቀሳቀስ እጅ ከፍንጅ በፖሊስ የተያዘ ሲሆን ተከሳሽ በፈፀመው ከባድ ስርቆት ወንጀል ዓቃቤ ህግ ክስ መስርቶበታል ። ጉዳዩ የተመለከተው የሀላባ ቁሊቶ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ተከሳሽን ጥፋተኛ ሲል በ6 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል ።

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 21፤2016 – በማዳጋስካር ምርጭ ፕሬዝዳንት ራጆኦሊና በድጋሚ አሸነፉ

የማዳጋስካር ሕገ-መንግሥታዊ ፍርድ ቤት ከሁለት ሳምንት በፊት የተካሄደውን አወዛጋቢ ምርጫ ተከትሎ ፕሬዚዳንት አንድሪ ራጆኤሊና በድጋሚ መመረጣቸውን አረጋግጧል። ፍርድ ቤቱ ራጆኤሊና ከተሰጠው ድምጽ 59 በመቶ የመራጮችንድ ድምፅ በማግኘት ለሶስተኛ ጊዜ መመረጣቸውን አስታውቋል። በምርጫው ተዓማኒነት ላይ ተቃዋሚዎች ያቀረቡትን ቅሬታ ውድቅ አድርጓል።

አብዛኞቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምርጫውን ውድቅ በማድረግ ተቀባይነት የለውም ብለዋል። “አንድሪ ራጆኤሊና የማዳጋስካር ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሆነው በመመረጥ ቃለ መሃላ መፈፀማቸውን የሕገ መንግሥት ፍርድ ቤት ኃላፊ የሆኑት ፍሎሬንት ራኮቶአሪሶአ ለሮይተርስ የዜና ወኪል ተናግረዋል።ከ 13 ፕሬዚዳንታዊ ተፎካካሪዎች አስሩ ካእጩነታቸውን ራሳቸውን አግለው በምርጫው ሳይሳተፉ ቀርተዋል።

በምርጫው ተዓማኒነት ላይ ስጋት በማንሳት ደጋፊዎቻቸው ድምጽ እንዳይሰጡ በመጠየቅ በደሴቲቱ ሀገር ታሪክ ዝቅተኛው የህዝብ ተሳትፎ የተደረገበት ምርጫ በሚልም ተመዝግቧል። በተጨማሪም ራጆኤሊናን ለሶስተኛ ጊዜ ለፕሬዝዳንትነት ለመወዳደር ያቀረቡትን ጥያቄ እና የእጩነቱን ትክክለኛነታቸው የፈረንሣይ ጥምር ዜግነት ያላቸው በመሆኑ ተቃዋሚዎች አውግዘዋል።

የሕገ መንግሥታዊ ፍርድ ቤት አስቀድሞ የራጆኤሊናን በድጋሚ ለሶስተኛ የሥልጣን ዘመን ለመወዳደር ያቀረቡትን ጥያቄ ውድቅ አድርጎ ነበር።የራጆኤሊና ሁለቱ የቅርብ ተቀናቃኞቻቸውን ስቴኒ ራንድሪያናሶሎኒያኮ እና የቀድሞ ፕሬዚደንት ማርክ ራቫሎማናናን በቅደም ተከተል 14% እና 12% ድምጽ አግኝተዋል።

ከምርጫው በፊት ለሳምንታት የዘለቀው ሰላማዊ ሰልፎች እና ከፖሊስ ጋር ግጭት የተፈጠረ ሲሆን ተቃዋሚዎች ራጆኤሊና ኢፍትሃዊ የምርጫ ሁኔታዎችን ፈጥረዋል ሲሉ ከሰዋል።ራጆኤሊና ግን ክሱን ውድቅ አድርገዋል። ዩናይትድ ስቴትስ እና የአውሮፓ ህብረት ፕሬዚዳንቱ እንዲነጋገሩ እና የምርጫ ማሻሻያዎችን እንዲያካሂዱ ዓለም አቀፍ ጥሪዎችን አድርገዋል ።

በሚሊዮን ሙሴ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 21፤2016 –በጋዛ ከሰባት ቀናት የተኩስ እረፍት በኃላ ጦርነት ተቀሰቀሰ

???? ባገረሻው ግጭት ከ70 በላይ ፍልስጤማውያን ተገድለዋል

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ በጋዛ ዳግም ጦርነት በመጀመሩ በጣም ተጸጽቻለሁ ብለዋል።

በማህበራዊ ድረ-ገፅ ላይ ባሰፈሩት መግለጫ መሰረት አሁንም የተኩስ አቁሙ ይመለሳል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ሲሉ ተደምጠዋል። ወደ ጦርነቱ መመለስ እውነተኛ ሰብአዊ የተኩስ አቁም ማድረግ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ብቻ ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል። ጋዛን የሚያስተዳድረው የሃማስ የጤና ሚኒስቴር እንዳስታወቀው እስራኤል የጦር ዘመቻዋን ከጀመረች ወዲህ ወደ 6,000 የሚጠጉ ህጻናትን ጨምሮ ከ14,800 በላይ ሰዎች ተገድለዋል ብለዋል።

በጥቅምት 7 ሃማስ በእስራኤል ላይ ጥቃት ሰንዝሮ 1,200 ሰዎችን ሲገድል 240 የሚጠጉ ሰዎችን አግቶ ወደ ግዛቱ መውሰዱ ይታወሳል።ባለፈው ሳምንት ከታጋቾቹ ውስጥ ከ100 በላይ የሚሆኑት የተለቀቁ ሲሆን ፍልስጤማውያን እስረኞችን ከእስራኤላውያን እስር ቤቶች ለማስለቀቅ ተችሏል።በእስራኤል እና በሃማስ መካከል ለሰባት ቀናት የዘለቀው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ያለተጨማሪ ማራዘሚያ ካበቃ በኋላ በጋዛ ጦርነቱ ቀጥሏል።

በመላው ጋዛ ከባድ የተኩስ ልውውጥ እና በርካታ ትላልቅ የአየር ድብደባዎች ታይተዋል እንዲሁም ተሰምተዋል። የእስራኤል ጦር እንዳስታወቀው ሮኬቶች በደቡብ እስራኤል ላይ ከጋዛ ሰርጥ ተተኩሰዋል። በጋዛ ታግተው የነበሩትን ሴት እና ህጻናትን ሙሉ በሙሉ ማስለቀቅ ባለመቻሉ ሃማስን የእስራኤል ጦር ተወቃሽ አድርጓል። እርቁ ከማብቃቱ በፊት ሮኬቶች ወደ እስራኤል ተተኩሰዋልም ብሏል።

ሀማስ በበኩሉ የተኩስ አቁም ስምምነቱን በማፍረስ እስራኤልን በመወንጀል የነዳጅ አቅርቦቶችን ወደ ሰሜን ጋዛ እንዳይደርስ አድርጋለች ብሏል።በጋዛ ሃማስ የሚመራው የጤና ሚኒስቴር ጦርነቱ ካገረሸ በኋላ ባሉት ሰአታት ውስጥ ቢያንስ 70 ሰዎች በአየር ድብደባ መገደላቸውን አስታውቋል ። በደቡባዊው ከተማ ከካን ዮኒስ በስተምስራቅ የሚገኙ ሰዎች በግብፅ ድንበር አቅራቢያ ወደምትገኘው ወደ ራፋህ እንዲሄዱ የሚያስጠነቅቅ በራሪ ወረቀቶች ተበትነዋል።

የእስራኤል የመከላከያ ሰራዊት ጋዛን በመቶዎች በሚቆጠሩ ዞኖች የሚከፋፍል አዲስ ካርታ የሰራ ሲሆን ይህም “ለቀጣዩ የጦርነት ደረጃ ዝግጁነት” ሰላማዊ ዜጎችን ለቀው እንዲወጡ የሚፈልጓቸውን አካባቢዎች ለማስጠንቀቅ ይጠቅማል ተብሏል።በኳታር የተኩስ አቁሙን ለማስቀጠል አስቸጋሪ የተባለው ድርድር እንደቀጠለ ምንጮች ተናግረዋል።

ጦርነቱ እንደገና ከመጀመሩ በፊት የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ለእስራኤል እንደተናገሩት በዚህ ጊዜ ሰላማዊ ዜጎችን በተለየ መንገድ መጠበቅ እስራኤል እንዳለባት ገልፃዋል።በሰሜን ጋዛ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የዜጎች ሞት እና የጅምላ መፈናቀል በደቡብም ሊደገም እንደማይገባም አሳስበዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህጻናት ኤጀንሲ እርቁ ካልቀጠለ በቀር ሰብአዊ ጥፋት እንደሚመጣ አስጠንቅቋል። በደቡባዊ ጋዛ በሚገኝ ሆስፒታል የዩኒሴፍ ቃል አቀባይ ሁኔታውን አስፈሪ ሱል ገልጿል።

በስምኦን ደረጄ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 21፤2016 – በኢትዮጽያ በዓመት ከ8 ሺህ በላይ ሰዎች በኤች አይ ቪ እንደሚያዙ ተገለፀ

በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ከ610 ሺ በላይ የሚሆኑ ግለሰቦች ኤች አይ ቪ ኤድስ በደማቸው ውስጥ እንደሚገኝ  እና በዓመት 8,257 ሰዎች ደግሞ  በቫይረሱ እንደሚያዙ የኤች አይ ቪ ኤድስ መከላከል እና ቁጥጥር መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ያደታ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን   ተናግረዋል።

በዛሬው እለት የዓለም የኤድስ ቀን የማህበረሰብ መሪነት ለላቀ ኤች አይ ቪን መከላከል በሚል መሪ ቃል በመላው ዓለም ታስቦ ውሏል። በኢትዮጵያ በዓመት ውስጥ በቫይረሱ ምክንያት የሚከሰት ሞት መጠን በ2010 ከነበረበት በ52 በመቶ መቀነስ መቻሉን ብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ከጤና ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያሳያል።

በ2022 በዓለም አቀፍ ደረጃ 39 ሚሊዮን ሰዎች  ኤች አይቪ በደማቸው እንደሚገኝ ከእነዚህም 630,000 የሚሆኑት ህይወታቸውን ማጣታቸው ተነግሯል። 1.3 ሚሊዮን የሚሆኑት ደግሞ  አዲስ የሚያዙ ሰዎች ሲሆኑ  ኢትዮጽያን ጨምሮ በመላው ዓለም በተሰራ ጥናት ሴቶች በቫይረሱ  ይበልጥ ተጠቂ  መሆናቸው ተጠቁሟል።

በ2025 ኤች አይ ቪ በደማቸውመገኘቱን የሚያውቁ ሰዎች ውስጥ 95በመቶ የሚሆኑትን የጸረ ኤች አይቪ ህክምና እንዲያገኙ ማድረግ እና ህክምና የጀመሩትን ክትትላቸውን በማስቀጠል በደማቸው ያለውን የቫይረስ መጠን ዝቅ በማድረግ ዙሪያ ትኩረት ተደርጎ እንደሚሰራ ተጠቁሟል።የኤች አይቪ ኤድስ ሰርጭት መጠኑ ከክልል ክልል የሚለያይ ሲሆን  ከፍተኛ የስርጭት መጠን የሚታይበት ቀዳሚው ክልል ጋምቤላ ሲሆን  አዲስ አበባ እና ሀረሪ ክልል የሁለተኛ እና ሶስተኛ ቦታዎችን ይዘው ይገኛሉ።

በሌላ በኩል ደግሞ ዝቅተኛ የስርጭት መጠን የሚታይበት ክልል ሶማሌ ክልል መሆኑን አቶ ፍቃዱ ያደታ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

በኤደን ሽመልስ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 21፤2016 -ከእስር የተፈቱት ፍልስጤማውያን በእስራኤል እስር ቤቶች ውስጥ ከፍተኛ በደል ይደርስባቸው እንደነበር ተናገሩ

ከእስራኤል እስር ቤት የተለቀቁ የፍልስጤም እስረኞች በጥቅምት 7 ሃማስ በእስራኤል ላይ ካደረሰው ጥቃት በኋላ ባሉት ሳምንታት ውስጥ በማረሚያ ቤት ጠባቂዎች እንግልት እና የጋራ ቅጣት ፈፅመውብናል ሲሉ ተናግረዋል። በዱላ መመታህ፣ ከውሾች ጋር እንድንቀመጥ መደረግን ጨምሮ ልብሳችን ፣ ምግብ እና ብርድ ልብስ እንደተወሰደባቸው ተናግረዋል። አንዲት ሴት እስረኛ አስገድዶ መድፈር መኩራ እንደተፈፀመባት ተናግራለች።

በእስር ቤት ውስጥ ባሉ እስረኞች ላይ ሁለት ጊዜ አስለቃሽ ጭስ እንደተተኮሰም። በቅርቡ ከእስር የተለቀቁ ስድስት ሰዎችን ቢቢሲ ያነጋገረ ሲሆን ሁሉም እስር ቤት ከመውጣታቸው በፊት ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ተናግረዋል። የፍልስጤም እስረኞች ማህበር አንዳንድ ጠባቂዎች እጃቸው በካቴና በታሰሩ እስረኞች ላይ ሽንታቸውን ይሸኑ እንደነበር ገልጿል። ባለፉት ሰባት ሳምንታት ውስጥ ስድስት ሌሎች እስረኞች በእስራኤል ማረሚያ ቤት ውስጥ ህይወታቸው አልፏል።

እስራኤል ሁሉም እስረኞች በህጉ መሰረት እንደታሰሩ ተናግራለች። የ18 አመቱ መሀመድ ናዝል በጋዛ በሃማስ ተይዘው በነበሩ በእስራኤላውያን ታጋቾች ምትክ በዚህ ሳምንት ከእስር ከተፈቱት መካከል አንዱ ነው። ከነሐሴ ወር ጀምሮ ያለምንም ክስ በማረሚያ ቤት ታስሮ እንደነበር እና ለምን እንደታሰረ እንደማያውቀው ተናግሯል።መሃመድ ከእስር ከተለቀቀ በኃላ በራማላህ በተደረገለት የኤክስ ሬይ ምርመራ በእስር ላይ እያለ በደረሰበት ድብደባ ጣቶቹ መሰበራቸውን ማረጋገጥ ተችሏል።

የፍልስጤም እስረኞች ማህበር ከጥቅምት 7 ጥቃት በኋላ በእስር ላይ የሚገኙት የፍልስጤማውያን ሞት ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን እና ከዚያን ቀን ጀምሮ ስድስት ሰዎች በእስር ቤት መሞታቸውን ተናግሯል። በዚህ ጉዳይ ላይ እስራኤል በቀጥታ ምላሽ ከመስጠት ተቆጥባለች። ነገር ግን ባለፉት ሳምንታት አራት እስረኞች በአራት የተለያዩ ቀናት መሞታቸውን እና የእስር ቤቱ አገልግሎት ስለ ሞት መንስኤ ምንም አያውቅም ብላለች ።

በስምኦን ደረጄ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 20፤2016 -በእየሩሳሌም በዛሬው እለት የደረሰው ጥቃት ከጋዛ ውጭ እየጨመረ ያለውን ውጥረት ሊያሳይ ይችላል ተባለ

በእየሩሳሌም ከተማ በዛሬው እለት የተፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ የሶስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በርካቶች ቆስለዋል።

ምናልባትም በእስራኤል እና በሃማስ መካከል እየተካሄደ ያለው ጦርነት በእስራኤል እና በፍልስጤም ግዛቶች ውስጥ ውጥረት ሊያነግስ እንደሚችል የሚያሳይ ነው ተብሏል። ሁለቱ ጥቃት አድራሾች ወንድማማቾች ሲሆኑ የእስራኤል የደህንነት አገልግሎት በምስራቃዊ እየሩሳሌም የሚገኙ የሀማስ ደጋፊዎች መሆናቸውን በመግለፅ በሽብር ተግባራቸው ቅጣት ይጠብቃቸዋል ተብሏል።

ከክስተቱ በኋላ ብዙም ሳይቆይ የእስራኤል ፖሊስ በአጥቂዎቹ መኪና ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያላቸውን ጥይቶች እና አውቶማቲክ ጠመንጃ የሚያሳዩ ምስሎችን አጋርቷል፣ ይህም ምናልባት በከተማው ውስጥ ሌላ ቦታ ላይ ሰፊ ጥቃት ለመሰንዘር አቅደው እንደነበር ይጠቁማሉ። ከሁለት ሳምንት በፊት በፍልስጤም ቤተልሄም እና እየሩሳሌም ከተሞች መካከል በሚገኝ የፍተሻ ጣቢያ ላይ በተፈጸመ የተኩስ ጥቃት አምስት እስራኤላውያን ሲቆስሉ አንድ የደህንነት መስሪያ ቤት አባል መገደሉ ይታወሳል።

ይህ የጥቃት ዜና የተሰማው በትላንትናው እለት የእስራኤል ጦር በጄኒን ከተማ ዘልቆ በገባበት ወቅት ሁለት ፍልስጤማውያን ወንድ ልጆች እድሜያቸው ስምንት እና 14 ዓመት የሆናቸው ታዳጊዎች በጥይት ከተገደሉ ከአንድ ቀን በኋላ ነው። ከጥቅምት 7 ወዲህ ከእስራኤል የጸጥታ ሃይሎች ጋር በተፈጠረ ግጭት በርካታ ፍልስጤማውያን ተገድለዋል።

በሌላ በኩል የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ለእስራኤል ፕሬዝዳንት አይዛክ ሄርዞግ ጋግ በዛሬው እለህ በቴል አቪቭ መክረዋል። ብሊንከን የእስራኤል-ሀማስ ጦርነት በጥቅምት 7 ከጀመረ ወዲህ ለሶስተኛ ጊዜ አካባቢውን እየጎበኛ ይገኛል።ባለፈው ሳምንት ታጋቾች ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ሲገናኙ የነበረውን አወንታዊ እድገት አይተናል ሲሉ ብሊንከን በስብሰባው ወቅት ተናግረዋል።

እንዲሁም የተኩስ አቁሙ በጋዛ ውስጥ ንጹሃን ዜጎች ወደሚፈልጉበህ እንዲሄዱ እና የሰብአዊ እርዳታ መጨመር አስችሏል ብለዋል። ይህ ሂደት ውጤቱን እያመጣ ነው፤ አስፈላጊ ነው እና ምሊቀጥል እንደሚችል ተስፋ እናደርጋለን ሲሉ ብሊንከን ተናግረዋል። ከእስራኤሉ ጠ/ሚ ቤንጃሚን ኔታንያሁ ጋር የተነጋገሩ ሲሆን ከፍልስጤሙ ፕሬዝዳንት ማህሙድ አባስን ጋግ በራማላ ይመክራሉ።

በበረከት ሞገስ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 20፤2016 -በከንባታ ጠንባሮ ዞን መምህራን የጥቅምት ወር ደሞዝ አልተከፈላቸውም ተባለ

???? ደሞዝ ባለመከፈሉ የተነሳ መምህራን ስራ አቁመዋል

በከንባታ ጠንባሮ ዞን ጠንባሮ ወረዳ ውስጥ ያሉ መምህራን የጥቅምት ወር ደሞዝ እንዳልተከፈላቸው የዞኑ አስተዳደር ገልጿል።

ዞን ከዚህ ቀደም በነበሩት ዕዳዎች የተነሳ ለደሞዝ የሚመጣው በጀት ተቆራርጦ እንደሚደርስ  የዞኑ አስተዳደር አቶ አበራ ኮርፊክሶ ለብስራት ሬድዮና ቴሌቭዥን በመናገር ችግሩ ውስብስብ መሆኑን አንስተዋል።

በተጨማሪም በጠንባሮ ወረዳ ያሉ ሙሉ የመንግስት ሰራተኞች ደሞዝ ከመስከረም ጀምሮ እንዳልተከፈላቸውም ተናግረዋል።ባለፈው 2015 በጀት ዓመት ጀምሮ የሰራተኞች የደሞዝ ወራት እያለፉ እንደተከፈላቸው እና ለደሞዝ ከተበጀው  ገንዘብ ውጪ በሌላ መንገድ የሚገኙ ገንዘቦችን ለደሞዝ በማከፋፈል እንደተከፈለም ገልፀዋል።

የበጀት እጥረቱ የተከሰተው ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በጥሬ ገንዘብ ብድር ደሞዝ ለሰራተኞች እንደተከፈለ እና በብድር የተከፈለውም ደሞዝ እስካሁን ድረስ የበጀት ጉድለት እንዲከሰት ማድረጉን ገልፀዋል። በዚህ ምክንያትን የሙድላ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን ስራ ማቆማቸውን ገልፀዋል።

የበጀት እጥረቱ አሁን ላይ ሊከሰት የቻለው ቀድሞ በነበረው ዕዳ ምክንያት ለማዳበሪያ እና ለጥሬ እህል እንዲሁም ለሌሎች ጉዳዮች ስለሚቆረጥ መሆኑን ጨምረው ለጣቢያችን ተናግረዋል።

በምህረት ታደሰ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 20፤2016 -ተሳፋሪ መስለው በመግባት አሽከርካሪውን የገደሉት ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ

ዮሃንስ ሰለሞን እና እዮብ በሃይሉ የተባሉት ተከሳሾች ወንጀሉን የፈፀሙት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታው ሳሪስ አቦ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው፡፡

ተከሳሾቹ ዛይራይድ ወደተባለ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ድርጅት ስልክ በመደወል ተሽከርካሪ እንዲመጣላቸው ካደረጉ በኋላ ከሳሪስ አቦ ወደ ጎተራ ከኋላ ወንበር ተቀምጠው ጉዞ ይጀምራሉ፡፡  ነገር ግን ጎተራ ከደረሱ በኋላ ምክንያት ፈጥረው በድጋሚ ወደመጡበት እንዲመልሳቸው ለአሽከርካሪው ይነግሩትና  ወደ ሳሪስ አቦ ይመለሳሉ፡፡

ወንጀል ለመፈፀም የሚያስችላቸውን ጨለማ እና ሰዋራ ስፍራ ሲያገኙ እዮብ የአሽከርካሪውን አንገት በገመድ ሲያንቀው ዮሃንስ ደግሞ በድብቅ ይዞት በነበረው መዶሻ  አናቱን በመምታት ህይወቱ እንዲያልፍ አድርገዋል፡፡

የአሽከርካሪውን መሞት ካረጋገጡ በኋላ ተሽከርካሪውን ጨምሮ  2ሞባይል ስልኮችንና ጥሬ ገንዘብ የወሰዱት ተከሳሾቹ፣ መኪናውን ለመሸጥ ሞክረው አልሳካ ሲላቸው ወርቁ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መንገድ ዳር አቁመው ተሰውረዋል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ  ወንጀሉ እንደተፈፀመ ሪፖርት ከደረሰው በኋላ  የምርመራና የክትትል ቡድን በማቋቋም ባደረገው ከፍተኛ ጥረት ተከሳሾቹ ከሶስት ወራት ፍለጋ በኋላ በቁጥጥር ስር ሊውሉ ችለዋል፡፡

ጉዳዩን ሲመለከት የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት ሰሞኑን በዋለው ችሎት ተከሳሾቹ በፈፀሙት ከባድ የውንብድና ወንጀል  ጥፋተኝነታቸውን  በሰው እና በሰነድ ማስረጃ ካረጋገጠ በኋላ  ዮሃንስ ሰለሞን  በ15 ዓመት እንዲሁም  እዮብ በሃይሉ በ12 ዓመት ፅኑ እስራ እንዲቀጡ ወስኗል፡፡

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 20፤2016 -የኖቤል ሽልማት አሸናፊ እና በጦር ወንጀለኝነት የተፈረጁት የቀድሞ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሄንሪ ኪሲንገር በ100 አመታቸው ከዚህ አለም በሞት ተለዩ

ሄንሪ ኪሲንገር  በ100 ዓመታቸው በኮነቲከት በሚገኘድ መኖሪያ ቤታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።በውጪ ግንኙነት ፖሊሲ ውስጥ ቁርጠኛ ባለሙያ የሚባሉ ሲሆን፣  የኖቤል የሰላም ሽልማት በአንድ ወገን ሲሸለሙ በሌላ በኩል ደግሞ የጦር ወንጀለኛ ተብለው ሙሉ በሙሉ ተወግዘዋል።

የዩናይትድ ስቴትስ ብሄራዊ ደህንነት አማካሪ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በመሆን ከሶቪየት ኅብረት እና ከቻይና ጋር ያለውን ግንኙነት በብርቱ የተከታተሉ እን የመሩ ሰው ናቸው። እኤአ በ1973 የአረብ-እስራኤል ግጭት እንዲቆም በዲፕሎማሲ ረገድ ሰርተዋል። የፓሪስ የሰላም ስምምነት ድርድር አሜሪካን በቬትናም ከነበረችበት ረጅም ቅዠት እንድትወጣ እስችለዋል።

ደጋፊዎቻቸው በአመራር ብቃታቸው እውነተኛ ፖለቲከኛ ሲሉ የሚያወድሷቸው ሲሆን ተቺዎቻቸው ደግሞ ግብረ ገብ የጎደላቸው ሲሉ ያወግዟቸዋል። በቺሊ ውስጥ የግራ መንግስትን የገለበጠውን ደም አፋሳሽ መፈንቅለ መንግስት በመደገፍ እና የአርጀንቲና ጦር በህዝቡ ላይ ያካሄደውን ‘ቆሻሻ ጦርነት’ የሚባለውም ውጊያ ዓይናቸው እያየ ቢያንስ በዝምታ በመደገፍ ተከሰዋል።

ኮሚዲያኑ ቶም ሌሬር ለቀድሞ ሚኒስትሩ ኪሲንገር የኖቤል ሽልማት መሰጠቱን ሲሰማ የፖለቲካ ሳታየር ወይም ፌዝ ጊዜ ያለፈበት ነው ማለቱ ይታወሳል።ሄንዝ አልፍሬድ ኪሲንገር በ1923 ባቫሪያ ውስጥ መካከለኛ ገቢ ካላቸው የአይሁድ ቤተሰብ ተወልደዋል። ቤተሰቡ የናዚን ስደት ለመሸሽ በ1938 ወደ ኒውዮርክ ወደ ሚገኘው የጀርመን-የአይሁድ ማህበረሰብ ተቀላቅለዋል።

ሄንሪ በተፈጥሮ ዓይን አፋር ታዳጊ የነበሩ ሲሆን ከፍተኛ የእግር ኳስ ፍቅር ነበራቸው። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በማታ የጨረሱ ሲሆን ቀን ቀን ብሩሽ ፋብሪካ ውስጥ ይሰሩ ነበር። አካውንቲንግ ለማጥናት አቅደው የነበረ ቢሆንም ሠራዊቱን ግን ተቀላቅለዋል። በእግረኛ ጦር ተመድበው የአእምሮ ብስለት እና የቋንቋ ችሎታቸው በወታደራዊ መረጃ ጥቅም ላይ ውሏል።  የ23 አመት ወጣት ተጠርጣሪዎችን የማሰር ፍፁም ስልጣን ያለው የቀድሞ የጌስታፖ መኮንኖችን የሚያድን ቡድን በቡልጌ ውጊያ ተሰጥቶት ነበር።

በእስካሁን አለማየሁ

መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 20፤2016 – የሰባ ዓመቷ ኡጋንዳዊት አዛውንት መንታ ልጆችን በሰላም ተገላገሉ

የ70 ዓመቷ ዩጋንዳዊት ሴት የመካንነት IVF ህክምና ከተደረገላቸው በኋላ መንታ ልጆችን ወልዳለች።

ህጻናትን የወለደችበት ሆስፒታል በአፍሪካ የመጀመሪያዋ ሴት ሆናለች ሲል ይፋ አድርጓል። በኡጋንዳ ዋና ከተማ ካምፓላ የሚገኘው የሴቶች ሆስፒታል ኢንተርናሽናል እና የወሊድ ማእከል ሳፊና ናሙኩዋያ የተባለችው የ70 ዓመት አዛውንት ወንድ እና አንዲት ሴት ልጅ እንደወለደች አስታውቋል።

ወ/ሮ ናሙክዋያ በተሳካ ሁኔታ መገላገላቸውን ተከትሎ ይህ ታሪክ በህክምና ስኬት ላይ ብቻ ሳይሆን በሰው ልጅ የመንፈስ ጥንካሬ ላይ ያተኮረ ነው ሲል ሆስፒታሉ በፌስቡክ ገፁ ላይ አጋርቷል። ወይዘሮ ናሙኩዋያ በ2020 በ67 ዓመታቸው ሴት ልጅ ከወለዱ በኃላ በሦስት ዓመታት ውስጥ  የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ እንደሆነ የዩጋንዳው ኤንቲቪ ቻናል ዘግቧል።

ወ/ሮ ናሙክዋያ በእርግዝና ወቅት ብዙ ችግሮች እንዳጋጠሟት ተናግራለች፣ ከእነዚህም መካከል የልጆቹ አባት ቤቱል ለቆ ጠፍቶ ነበር ብላለች። ለወንዶች ከአንድ በላይ ልጅ ነፍሰ ጡር እንደሆንክ ስትነግራቸው አይወዱም እኔ መንታ ልጆችን ማርገዜን ከነገርኩት ጊዜ ጀምሮ የኔ ሰው መጥቶ አያውቅም ብላለች።

ወይዘሮ ናሙኩዋያ ልጆቹን እንዴት ማሳደግ እንደምትችል እንደማታውቅ ትገልጻለች። ገር ግን ልጅ አልባ በመሆናችን የተነሳ ለብዙ አመታት ከዘለቀው መገለል እና መሳለቂያ ከመሆናችን በኃላ በመሆኑ ደስተኛ ነኝ ብላለች።

ልጅ ሳላገኝ እንድሞት በእናቴ ተረግሜአለሁ ብዬ አስብ ነበር ስትል አክላለች።

በስምኦን ደረጄ