መደበኛ ያልሆነ

ኢትዮጵያና ደቡብ ኮሪያ የ264 ሚሊዮን ዶላር የቀላል ብድር ስምምነት መፈራረማቸው ታውቋል

የደቡብ ኮሪያ ኤክስፖርትና ኢምፖርት ባንክ (EXIM BANK) በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚከናወኑ የልማት ፕሮክቶች የሚውል የ264 ሚሊዮን ዶላር የቀላል ብድር ለማቅረብ የሚያስችል የማዕቀፍ ስምምነት በገንዘብ ሚኒስቴር ተደርጓል፡፡

የመጀመሪያው የ170 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት በደቡብ ኢትዮጵያ ለሚገኘው የብሔራዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍሰትና የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ፕሮጀክት የሚውል እንደሆነ በገንዘብ ሚኒስትር የህዝብ ግንኙነት ባለሞያ የሆኑት አቶ ሃጂ ኢብሳ ለብስራት ተናግረዋል፡፡

በዚህም በሰሜን ምዕራብ ለሚገኙ የሀገሪቱ ክፍሎችና እና ለኦሞ ስኳር ፋብሪካ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ሀይል ለማቅረብ ያስችላል ተብሏል፡፡

ተጨማሪም ለአርባምንጭ ኢንዲስትሪያል ፓርክ እንደሚውል ተነግሯል፡፡

የሁለተኛው የ94 ሚሊዮን ዶላር የቀላል ብድር ስምምነት በሀገሪቱ ውስጥ ለሚስሩ የመስኖ ልማትና የገጠር ልማት ፕሮጀክቶች እንደሚውል ተጠቅሷል፡፡

አርሶ አደሩ የግብርና ምርቱን እንዲያሳድግና ገቢው እንዲጨምር ያደርጋል መባሉንም አቶ ሃጂ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡

 

ፍሬህይወት ታደሰ

 

መደበኛ ያልሆነ

ሴት ሰራተኞች

የህፃናት ማቆያን በከፈቱ የመንግስት ተቋማት አገልግሎት የሚሠጡ ሴት ሰራተኞች ለልጆቻቸው የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲጠቀሙ መደረጉ ተነገረ፡፡

 

የሴቶች ፤ ህፃናትና ወጣቶች ጉዳይ ሚኒስቴር የመንግስት ሰራተኛ እናቶች የህፃናት ማቆያ አገልግሎት እንዲያገኙ ባደረገዉ ጥረት አገልግሎቱ በተወሰኑ መስሪያ ቤቶች እንዲሰጥ መደረጉ ይታወሳል፡፡

ሆኖም ወደ ማቆያዉ ልጆቻቸዉን ይዘዉ ሲመጡ ከፍተኛ የትራንስፖርት ችግር ስለሚገጥማቸሁ ለከፋ እንግልት መዳረጋቸዉንም ተጠቃሚዎቹ ይናገራሉ፡፡

 

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የሴቶች ሕጻናትና ወጣቶች ጉዳይ ሚኒስቴር ከፍተኛ የኮምኒኬሽን ባለሙያ አቶ መላኩ ባዩ ለብስራት ሬድዮ እንደተናገሩት ችግሩን ከግምት ዉስጥ በማስገባት ሚኒስቴር መ/ቤቱ የፐብሊክ ትራንስፖርት አገልግሎት ከህፃናት ልጆቻቸዉ ጋር እንዲያገኙ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሲሰራ ቆይቷል፡፡

በዚሁ መሰረትም የፐብሊክ ሰርቪስ ሰራተኞች የትረንስፖርት አገልግሎት ድርጅት ባደረገዉ ትብብር ቅድመ-ሁኔታዎችን ለሚያሟሉ ሴት የመንግስት ሰራተኞች የትራንስፖርት አገልግሎቱ እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡

አቶ መላኩ ለብስራት ሬድዮ እንደነገሩን የጠቀመጡት ቅድመ ሁኔታዎች በሚሰሩበት መስሪያ ቤት የሕፃናት ማቆያ መቋቋሙን የሚገልጽ ደብዳቤ፡፡
የሕጻኑ/የሕጻንዋ የልደት ሰርተፍኬት ፎቶኮፒ በሚሰሩበት መ/ቤት ሰው ሃይል ከዋናው ጋር ተመሳክሮ በኃላፊ ተፈርሞ እና የመ/ቤቱ ማህተም ተደርጎበት መቅረብ ይኖርበታል፡፡

ሕጻን ይዛ የምትጓጓዘው ሴት የፐብሊክ ሰርቪስ ሠራተኛ መረጃ ተ.ቁ ፤ ሙሉ ስም ከነአያት፤ የመኖርያ አድራሻ ፤ክፈለከተማ፤ የቤትቁጥር ፤ታክሲ ወይም አውቶቡስ የምትሳፈርበት ቦታ ልዩ ስም፤ ሞባይል ስልክ ቁጥር፤ የመ/ቤት ስምና መ/ቤት የሚገኝበት ቦታ ልዩ ስም በቅጹ ተሞልቶ በሸኝ ደብዳቤ ማህተምና ፊርማ ተደርጎበት በሰውሃብት ባለሙያዎች ለየፐብሊክ ሰርቪስ ሰራተኞች የትረንስፖርት አገልግሎት ድርጅት እንዲላክ እና ለዚህ የተዘጋጀ ልዩ መታወቂያ እንዲዘጋጅላቸው ማድረግ እንደሚገባም ተጠቁሟል፡፡

 

በማህሌት ካሳሁን