የደቡብ ኮሪያ ኤክስፖርትና ኢምፖርት ባንክ (EXIM BANK) በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚከናወኑ የልማት ፕሮክቶች የሚውል የ264 ሚሊዮን ዶላር የቀላል ብድር ለማቅረብ የሚያስችል የማዕቀፍ ስምምነት በገንዘብ ሚኒስቴር ተደርጓል፡፡
የመጀመሪያው የ170 ሚሊዮን ዶላር የብድር ስምምነት በደቡብ ኢትዮጵያ ለሚገኘው የብሔራዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍሰትና የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ፕሮጀክት የሚውል እንደሆነ በገንዘብ ሚኒስትር የህዝብ ግንኙነት ባለሞያ የሆኑት አቶ ሃጂ ኢብሳ ለብስራት ተናግረዋል፡፡
በዚህም በሰሜን ምዕራብ ለሚገኙ የሀገሪቱ ክፍሎችና እና ለኦሞ ስኳር ፋብሪካ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ሀይል ለማቅረብ ያስችላል ተብሏል፡፡
ተጨማሪም ለአርባምንጭ ኢንዲስትሪያል ፓርክ እንደሚውል ተነግሯል፡፡
የሁለተኛው የ94 ሚሊዮን ዶላር የቀላል ብድር ስምምነት በሀገሪቱ ውስጥ ለሚስሩ የመስኖ ልማትና የገጠር ልማት ፕሮጀክቶች እንደሚውል ተጠቅሷል፡፡
አርሶ አደሩ የግብርና ምርቱን እንዲያሳድግና ገቢው እንዲጨምር ያደርጋል መባሉንም አቶ ሃጂ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል፡፡
ፍሬህይወት ታደሰ