መደበኛ ያልሆነ

ህገ ወጥ የስንፈተ ወሲብ መድኃኒቶች በገበያ ላይ መዋላቸው ተገልጿል፡፡

ህገ ወጥ የስንፈተ ወሲብ መድኃኒቶች በገበያ ላይ መዋላቸው ተገልጾል፡፡

የኢትዮጵያ የምግብ መድኃኒትና የጤና ክብካቤ አስተዳደርና ቁጥጥር ባለስልጣን በድህረ ገበያ ቅኝት ባደረገው የቁጥጥር ስራ ያልተመዘገቡ፣ ጥራት እና ደህንነነታቸው ያልተረጋገጡ በህገወጥ መንገድ ወደሀገር ውስጥ የገቡ የስንፈተ ወሲብ መድሃኒቶች ማግኘቱን የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የህዝብ ግንኙነት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሳምሶን አብርሀም ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል፡፡ መደኃኒቶች ህጋዊ መሆን አለመሆናቸውን ለመለየት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ስርዓት የዘረጋ ሲሆን ይሄም የመድኃኒቱን ስም በwww.mris.fmhaca.gov.et በሚለው ዌብሳይት በማስገባት መድኃኒቱ መመዝገብ አለመዝገቡን እና ሌሎች ከመድኃኒቱ ጋር ተየያዥነት ያላቸው መረጃዎችን ማግኘት እንደሚቻል ተገልጿል፡፡ ስለሆነም ማህበረሰቡ መሰል ተግባር ሲፈፀም ከተመለከተ በአከባቢያቸው ላሉት ተቆጣጣሪ አካላት አሊያም ለጤና ቢሮ እና ለፖሊስ በተጨማሪም በነጻ ስልክ መስመር 8482 በመደወል ለባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እንዲያሳውቅ አቶ ሳምሶን አሳስበዋል፡፡ ፍሬህይወት ታደሰ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *