መደበኛ ያልሆነ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን ጨምሮ የተለያዩ ተቋማት ተሳታፊ የሆኑበትና በአፍሪካ ዘላቂ የሰላም እና ደህንነት ጉዳይ ላይ የሚመክር ስብሰባ በአዲስ አበባ ተካሄደ፡፡

መቀመጫውን አዲስ አበባ ባደረገው የደህንነት ጥናት ኢኒስቲትዮት የተዘጋጀውን ስብሰባ በንግግር የከፈቱት የተቋሙ ዳይሬክተር ዶ/ር ሮባ ሽራም ናቸው፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ ፅ/ቤት ለብስራት ሬድዮ በላከው መግለጫ፡- በአፍሪካ የሚከሰቱ የሰላም እና ደህንነት ፈተና ለመፍታት የተቀናጀ እና ፈጠራ የታከለበት እርምጃ መውሰድ እንደሚገባም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡

የአይ.ኤስ.ኤስ አመራር ቦርድ ፕሬዝዳንት ሰኢድ ጂኔት በበኩላቸው በአህጉራቱ የሚከሰቱ ችግሮችን ለመቅረፍ በአፍሪካ ህብረት እና ክፍለ አህጉራዊ ድርጅቶች መሀከል የተቀናጀ ጥረት ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡ተሳታፊዎችም በኢትዮጵያ እየተካሄደ ያለውን ፈጣን ለውጥ አድንቀዋል፡፡

ስምኦን ደረጄ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *