መደበኛ ያልሆነ

የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ ከወቅቱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች ቡድን ዲን ጋር ተወያዩ

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው በትናንትናው እለት በኢትዮጵያ የጅቡቲ አምባሳደር እና የወቅቱ የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት አምባሳደሮች ቡድን ዲን የሆኑትን አምባሳደር ሙሃመድ እድሪስ ፋራህን በጽ/ቤታቸው ተቀበለው አነጋግረዋል።

ሚኒስትሩ የሀገሪቷ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ እንደሚሰጥ ጠቅሰው ኢትዮጲያ ከጅቡቲ ጋር ላላት ግንኙነት ልዩ ቦታ እንዳላት ገልጸዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ፅ/ቤት ለብስራት በላከው መግለጫ መሰረት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ስትራቴጅያዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላልም ብለዋል።

አምባሳደሩ በበኩላቸው ሚኒስትሩ በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በማነጋገራቸው አመስግነው የሀገራቱን ስትሬቴጅያዊ ግንኙነት በሁሉም ዘርፍ አጠናክረው ለማስቀጠል ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

ስምኦን ደረጄ

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *