መደበኛ ያልሆነ

መጋቢት 25፤2012- ብስራት የምሽት አጫጭር መረጃዎች

አጫጭር መረጃዎች

~ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል ከቤት መውጣትን የከለከለችው ቱኒዚያ በመዲናዋ ቱኒስ የሮቦት ፖሊስ ወደ ስራ አስገባች።ሮቦቱ የዜጎችን እንቅስቃሴ ይከታተላል።በቱኒዚያ በቫይረሱ ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር 14 ደርሷል።

~ የኢራን ግዙፉ አየርመንገድ ኤር ኢራን በኮሮና ቫይረስ ስጋት በጀርመን የሚያደርገውን በረራ በሙሉ ሰረዘ።

~ በደቡብ አፍሪካ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የወጣውን ህግ የተላለፉ ከ17ሺ በላይ ዜጎች በአንድ ሳምንት ውስጥ ብቻ መታሰራቸው ተሰማ።በደቡብ አፍሪካ 1,500 የሚጠጉ ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል።

~ አርጀንቲና በኮሮና ቫይረስ የተነሳ ወደ አውሮጳ ሀገራት ትልከው የነበረው የበሬ ስጋ ግብይት በመቀዛቀዙ ክፉኛ መጎዳቷ ተገለፀ።

~ እንደ ፔሩ ሁሉ ፖናማም ለግብይት ከቤት መውጣት የሚቻለው በጾታ ነው ስትል አስታወቀች።ሰኞ፣እሮብና አርብ ለወንዶች ማክሰኛ፣ሀሙስ እና ቅዳሜ ገበያ መሄድ የሚችሉት ሴቶች ብቻ ናቸው።አስቀድማ ከፓናማ ፔሩ ይህንን ህግ አውጥታለች።

~ የሜክሲኮ ፕሬዝዳንት አንድሬስ ማኑኤል ኦብራዶር በኮሮና ጊዜ በወንጀለኛ ቡድኖች የሚፈፀሙ ወንጀሎች በሜክሲኮ ስጋት እየፈጠሩ መሆኑን አስታወቁ።

~ በካናዳ በኮሮና ቫይረስ የተነሣ ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቁጥር 173 ሲደርስ የተጠቂዎች ቁጥር 11,747 መድረሱን የካናዳ መንግስት አስታውቋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *