ጦማር/ዜና

ሚያዝያ 14፣ 2012-በጡት ማስያዣዋ ዉስጥ ለ35 ቀናት የዳክዬ እንቁላል እንዲቀመጥ በማድረግ እንዲፈለፈል ያደረገችዉ እናት አድናቆት እየተቸራት ይገኛል

የካሊፎርኒያ ነዋሪ የሆነችዉ እናት ከሶስት ልጆቿ ጋር በመሆን በአንድ ፓርክ ዉስጥ ጉብኝት እያደረገች ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ታዲያ የዳክዬ ጎጆ ፈራርሶ ይመለከታሉ፡፡

በጡት ማስያዣዋ ዉስጥ ለ35 ቀናት የዳክዬ እንቁላል እንዲቀመጥ በማድረግ እንዲፈለፈል ያደረገችዉ እናት አድናቆት እየተቸራት ይገኛል፡፡

በርከት ያሉ የዳክዬ እንቁላል ተሰባብሮ የነበረ ሲሆን አንዱ እንቁላል ግን ስንጥቅ ብቻ አጋጥሞታል፡፡

በዚህ ጊዜ እናት ሮዝ ከልጆቿ እንቁላሉን እንድታድነዉ ጥያቄ ይቀርብላታል፡፡

እናትም ሳታቅማማ ለ35 ቀናት እንቁላሉን በጡት ማስያዣዋ በመታቀፍ ዳክዬ እንዲፈለፈል አድርጋለች፡፡ ስትተኛ ሁሉ እንቁላሉን ታቅፋ ትተኛ እንደነበረ ተነግሯል፡፡

እንቁላሉ ለመፈልፈል በቂ ሙቀት የሚያስፈልገዉ መሆኑን ተከትሎ ይህንን እርምጃ እናት መዉሰዷን ተናግራለች፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *