ጦማር/ዜና

ሚያዝያ 14፣ 2012 -አይኤስ(ዳኢሽን) ተቀላቅሎ የነበረዉ ራፐር በስፔን በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰማ

አይኤስ(ዳኢሽን) ተቀላቅሎ የነበረዉ ራፐር በስፔን በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰማ

ነዋሪነቱ በለንደን የነበረዉ የ28 ዓመቱ አብደል ማጂድ አብድለ ባሪ በ2013 በአይኤስ ፕሮፖጋንዳ ተማርኮ ለንደንን ጥሎ ወደ ሶርያ በማቅናት ቡድኑን ይቀላቀላል፡፡

አይኤስ(ዳኢሽ) የተለያዩ ምስሎችን በማህበራዊ ገጽ ሲለቅም ይህዉ ሰዉ በብዛት ይታይ ነበር፡፡የቡድኑን መዳከም ተከትሎ ዳግም በህገወጥ መልኩ ከሶርያ ስፔን ይገባል፡፡በስፔን አልሜሪያ ከጓደኞቹ ጋር በድብቅ ተከራይቶ ከሚኖርበት አፓርታማ በፖሊስ በቁጥጥር ስር ዉሏል፡፡

የአደል ባሪ ወላጅ አባት እ.ኤ.አ በ1998 በኬንያና ታንዛኒያ የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲዎች በአል ቃይዳ በደረሱ ጥቃቶች ጥፋተኛ መባላቸዉ ይታወሳል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *