ከአንድ ወር በፊት የ39 ዓመቷ ኦሶሪዮ የግዳጅ ለይቶ ማቆያ በኮሎምቢያ ሲተገበር በቂ የሚባል ገንዘብ ስላልነበራት ራሷን እንድታቆይ የተገደደችዉ መንግስት ባዘጋጀዉ መጠለያ ዉስጥ ነበር፡፡
መጠለያዉ የቡና እርሻ ባለበት የኮሎምቢያ ግዛት ዉስጥ ነዉ፡፡የ72 ዓመቱ አርዲላ የግንባታ ባለሙያ ሲሆን በኮሮና ምክንያት ስራ ቀዝቅዟል፤ከዚህም በተጨማሪ የጭንቀላት ጉዳት አጋጥሞት የቤት ኪራይ መክፈል ባለመቻሉ ወደ መጠለያ ለመግባት ይገደዳል፡፡
በዚህ ስፍራ ሳለ ታዲያ ስለ እርሱ ማንም ግድ እንደማይሰጠዉ ይናገራል፡፡ሆኖም ግን ይህቺ ሴት ስለ እርሱ መጨነቋ ይበልጥ ትኩረቱ ይስበዋል፡፡ይህ መተሳሰብ እና መቀራረብ ወደ ፍቅር አድጎ በቀናት ልዩነት በጋብቻ ተጣምረዋል፡፡
በዚሁ የመጠለያ ስፍራ ጋብቻቸዉን የፈፀሙ ሲሆን በመጠለያዉ የተለየ ስፍራ ለጥንዶቹ መሰጠቱ ተሰምቷል፡፡