የሴራሊዮን ፕሬዚዳንት የግል ጠባቂ በኮሮና ቫይረስ መያዙን ተከትሎ ፤ ፕሬዚደንቱ ራሳቸውን እንዲያገሉ ሆኗል።
ፕሬዚዳንት ጁሊየስ ማዳ_ባዮ የግል ጠባቂያቸው በቫይረሱ መጠቃቱን ተከትሎ ለአስራ አራት ቀናት የሚደረግላቸው ክትትል ካሳለፍነዉ ሰኞ ጀምረዋል።
እርሳቸው ለይቶ ማቆያ ላይ ቢሆኑም እንኳ የሚደረጉ የቅድመ ጥንቃቄ ስራዎች እንደማይቋረጥ ፤ ሃሳብ አይግባችሁ ሲሉ ለሴራሊዮናውያን በአይሀራሪ የዜና ወኪል በኩል አስታውቀዋል።
በእርሳቸውና ቤተሰባቸው ላይ እስካሁን ምንም አይነት ምልክት አለመታየቱንና ፤ በፍፁም ጤና ላይ እንደሚገኙም ገልፀዋል።