ሐሰተኛ መረጃን በማሰራጨት በሚል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩት እና ጉዳያቸው በፍርድ ቤት ሲታይ የቆየው ጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ ዛሬ ሚያዚያ 15/2012 ከዕስር መለቀቃቸውን የጋዜጠኛው ጠበቃ ታደለ ገብረመድሕን ለአዲስ ማለዳ አስታወቁ።
ጋዜጠኛው በ15 ሽሕ ብር ዋስ ከእስር ወጥተው ጉዳያቸውን በውጭ ሆነው እንዲከታተሉ ፍርድ ቤቱ ወስኗል። ጋዜጠኛው ከዚህ ቀደም ኹለት ጊዜያት የዋስትና መብታቸው በፍርድ ቤት ተከብሮላቸው እንዲወጡ ተወስኖ እንደነበር የሚታወስ ነው።