ጦማር/ዜና

ሚያዝያ 15፣2012-አሜሪካን ግቢ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ሸራ ወጥረው ህገ ወጥ- ቤት በመስራት 20 ሰዎችን በቤቱ ሰብስቦ ሺሻ ሲያስጨስ የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል

የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማናቸውም ቦታ የሺሻ ማስጨስና የጫት ማስቃም አገልግሎት መስጠትን ይከለክላል፡፡ግለሰቡ ግን የአዋጁን ክልከላ በመጣስ ለኮሮና ቫይረስ ስርጭት መስፋፋት ምክንያት የሚሆን ድርጊት ሲፈፅም እና ሲያስፈፅም ከ30 በላይ ከሚሆኑ የሺሻ ማጨሻ ዕቃዎች ጋር እጅ ከፍንጅ ተይዞ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታዉቋል፡፡

በተመሳሳይ ዜና በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው ጎማ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በተለያዩ ሁለት ቦታዎች በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ሺሻ ሲያስጨሱ የተገኙ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ የመርካቶ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል ምርመራ ቲም ሀላፊ ምክትል ኢንስፔክተር እሱባለው ጌትነት ገልፀዋል፡፡ በሁለቱ መኖሪያ ቤቶች 15 ሰዎች ሺሻ ሲያጨሱ የተገኙ ሲሆን 66 የሺሻ ማጨሻ ዕቃዎች ተይዘዋል፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *