አሜሪካ በፐርሺያ ቀጠና የደህንነት ችግር የምትፈጥር ከሆነ የጦር መርከቦቿን ኢራን እንደምታወድም አስጠነቀቀች
የኢራን ዋና ጄነራል ሆስኒ ሳላሚ እንደተገሩት በፐርሺያ ቀጠና የደህንነት ችግር አሜሪካ የምትፈጥር ከሆነ የኢራን የባህር ሀይል በአሜሪካ የጦር መርከቦች ላይ እርምጃ እንዲወስድ ትዕዛዝ አስተላልፌለዉ ብለዋል፡፡
በትላንትናዉ እለት ዶናልድ ትራምፕ በፐርሺያ ባህረ ሰላጤ የኢራን መርከቦች ማንኛዉንም አይነት ትንኮሳ ካደረሱ የአሜሪካ የባህር ሀይል እርምጃ እንደሚወስድ መናገራቸዉ ይታወሳል፡፡