ጦማር/ዜና

ሚያዝያ 16፣2012-የቤት ሰራተኛዉን ለመሸጥ ማስታወቂያ በፌስቡክ ያወጣዉ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ

ነዋሪነቱ በሊባኖስ የሆነዉና የሶርያ ዜግነት ያለዉ አሰሪ የናይጄሪያ ዜግነት ያላትን የቤት ሰራተኛዉን ለመሸጥ በፌስቡክ ማስታወቂያ ያወጣል፡፡የ30 ዓመት እድሜ ያላት ግለሰቧ በ1ሺ የአሜሪካ ዶላር ለሽያጭ ቀርባለች፡፡

ድርጊቱ በማህበራዊ ገጽ ትስስር ሲዘዋወር የተመለከተዉ በሊባኖስ የናይጄሪያ ኤምባሲ ጉዳዩን ለሊባኖስ መንግስት ያሳዉቃል፡፡ድርጊቱን የፈጸመዉ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዉሏል፡፡

በኩዌት በጥቁር ገበያ በማህበራዊ ገጽ ትስስር አማካኝነት የቤት ሰራተኞችን እንደሚሸጡ መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *