ጦማር/ዜና

ሚያዝያ 17፣ 2012-መንትያ እህትማማቾቹ በኮሮና ቫይረስ ህወታቸዉ አለፈ

ኬቲ እና ኤማ ዴቪስ የተባሉት መንትያ አህትማማች በሶስት ቀናት ልዩነት ዉስጥ በኮሮና ቫይረስ ህይወታችዉን አጥተዋል፡፡

ባሳለፍነዉ አርብ በሳዉዝአፕተን ጠቅላላ ሆስፒታል የ37 ዓመት እድሜ ያላት ኤማ ህይወቷ ያለፈ ሲሆን ባሳለፍነዉ ማክሰኛ ደግሞ ኬቲ ህይወቷን አጥታለች፡፡

ሌላኛዋ እህታቸዉ ዞኢ ስለዚሁ ሁኔታ ተጠይቃ ስትናገር ሁሌም አብረን ወደዚህች ምድር መጥተናል አብረን እንሄዳለን ሲሉ ይናገሩ ነበረ ብላለች፡፡

ኬቲ በህጻናት ሆስፒታል ዉስጥ በነርስነት ሙያ ትሰራ የነበረ ሲሆን ኤማ በቀድሞ ሙያዋ ነርስ ነበረች፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *