
በመላዉ ዓለም በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸዉን ያጡ ሰዎች ቁጥር ከ200ሺ በላይ ደረሰ
በዛሬዉ እለት በኮሮና ቫይረስ ህይወታቸዉን ያጡ ሰዎች ቁጥር ከ200ሺ በላይ ሲደርስ አሜሪካ፣ጣልያን፣ስፔን፣ፈረንሳይና እንግሊዝ ከ20ሺ በላይ ዜጎቻቸዉን በቫይረሱ የተነጠቁ ሀገራት መሆናቸዉን የጆን ሆፕኪንስ ዩኒቨርስቲ ይፋ አድርጓል፡፡
ከ2.8 ሚሊየን በላይ ሰዎች በቫይረሱ ሲያዙ 820ሺ የሚጠጉ ዜጎች አገግመዋል፡፡