መደበኛ ያልሆነ

ሚያዝያ 21፣2012-በኢትዮጵያ ከኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 130 ደርሷል

ባለፏት 24 ሰዓታት አራት ኢትዮጲያዉያን በቫይረሱ መያዛቸዉ ተረጋግጧል

የታማሚዎች ዝርዝር ሁኔታ፡-

~ ባለፉት 24 ሰዓት ዉስጥ ለ766 ሰዎች ምርመራ ተደርጎ በአራትት ግለሰቦች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል፡፡

~ ታማሚ አንድ ኢትዮጲያዊት ሴት እደሜ 18 ከፑንት ላንድ የተመለሰችና በጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ በለይቶ ለይቶ ማቆያ ዉስጥ የነበረች

~ ታማሚ ሁለት ኢትዮጲያዊት ሴት እድሜ 25 ከፑንት ላንድ የተመለሰችና በጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ በለይቶ ለይቶ ማቆያ ዉስጥ የነበረች

~ ታማሚ ሶስት ኢትዮጲያዊት ሴት እድሜ 15 ከፑንት ላንድ የተመለሰችና በጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ በለይቶ ለይቶ ማቆያ ዉስጥ የነበረች

~ ታማሚ አራት ኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሀረርጌ ዞን ጉባ ኮሪቻ ወረዳ ወንድ እድሜ 23 የዉጪ ሀገር ጉዞ የሌለዉ በበሽታዉ ከተያዘ ሰዉ ጋር ንኪኪ እንዳለዉ በመጣራት ላይ ይገኛል፡፡

ተጨማሪ መረጃ ፡-

~ አጠቃላይ ምርመራ የተደረገላቸው ሰዎች ቁጥር 16,434 ደርሷል።

~ ባለፉት 24 ሰዓት ተጨማሪ ስምንት ሰዎች አገግመዋል፡፡

~ አጠቃላይ ያገገሙ ግለሰቦች 58 ደርሰዋል

~ በጽኑ ህሙማን ማከምያ ዉስጥ የሚገኝ ታማሚ የለም፡፡

~ በለይቶ ህክምና ውስጥ ያሉ 67 ናቸው።

~ የሶስት ሰዎች ህይወት ማለፉ ይታወሳል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *