
ቡሃሪ ለመንግስት ኤጀንሲ የቦርድ አባላት የ37 ሰዎችን ስም ይፋ ሲያደርጉ ከነዚህ መካከል ከሁለት ወር በፊት ህይወቱ ያለፈ ሰዉ ተካቶበታል፡፡ቡሃሪ ለሹመት ያጩቸዉን ሰዎች የናይጄሪያ ሴኔት እንዲያጸድቅላቸዉ ከላኩ በሃላ የግለሰቡን ህልፈት ተገንዝበዋል፡፡
ኦኩሩ የተባለዉን እና ህይወቱ ያለፈ ሰዉን ለሹመት ማጨታቸው በናይጀሪያ የማህበራዊ ገጽ ትስስት ተጠቃሚዎች ዘንድ አግራሞት ፈጥሯል፡፡ቡሃሪ እንዲህ ዓይነት ስህተት ሲሳሳቱ የአሁኑ የመጀመሪያቸዉ አይደለም እ.ኤ.አ በ2017 ተመሳሳይ ስህተትን መፈጸማቸዉ ይታወሳል፡፡