መደበኛ ያልሆነ

ሚያዝያ 23፣2012-በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ሰኳርን ከተለያዩ ባዕድ ነገሮች ጋር በመቀላቀል ማር ነው በማለት ሲያዘጋጁ የነበሩ ሁለት ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ገለፀ።

ተጠርጣሪዎቹ የወንጀል ድርጊቱን ሲያከናውኑ የነበረው በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ልዩ ቦታው በተለምዶ ፋንታ ሰፈር እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ ነው።

ተጠርጣሪዎቹ ማሩን ለማዘጋጀት የሚጠቀሙባቸውን በረዶ መሰል ኬሚካል፣ቀይ እና ነጭ ዱቄት መሰል ፓውደር፣ እንጉዳይ መሰል እና 5 ኩንታል ሰኳር በአምሰት በርሜል ሲዘጋጅ የነበረ ማር እና ተዘጋጅቶ ለገበያ ሊውል የነበረ ዘጠኝ ማዳበሪያ ማር መሰል ተይዟል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *