መደበኛ ያልሆነ

ሚያዝያ 27፣2012-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ከወሎ ሰፈር—ኡራኤል እየተደረገ ያለውን የመንገድ ግንባታ ተመልክተዋል።

35 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ከወሎ ሰፈር ኡራኤል እየተገነባ ያለው መንገድ 1ነጥብ 4 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለውና በአንድ ጊዜ 6 የተሽከርካሪዎችን ማጓጓዝ የሚያስችል ነው ተብሏል።

ከመንገድ ግንባታው ጋር በተያያዘ ሲነሱ የነበሩ የወሰን ማስከበር ችግሮች መፍትሄ ማግኘታቸው ና ግንባታው ከግማሽ በላይ መጠናቀቁም ነው የተገለጸው።

በቅርብ ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህ መንገድ የብስክሌት መንገድንም ያካተተ መሆኑን ከከንቲባ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *