በዛሬው እለት በኔዘርላንድ አምስተርዳም በግፍ ህይወቱን በአሜሪካ ላጣው ጆርጅ ፍሎይድ አጋርነት ለማሳየት ሰልፍ ተካሂዷል።10ሺ የሚጠጉ ሰልፈኞች በአምስተርዳም ዳም አደባባይ በመገኘት ድምፃቸውን አሰምተዋል።
ፍትህ ከሌለ ሰላም የለም፣የጥቁር ህይወት ዋጋ አለው ያሉ ሰልፈኞች የትራፊክ እንቅስቃሴውን በመግታት ተቃውመዋል።የ44 ዓመቱ የፖሊስ አባል ድሬክ ቻዩቪን በ500ሺ የአሜሪካን ዶላር ዋስ ተጠይቆበት ከ8 ቀናት በኃላ ፍርድቤት ይቀርባል።
ስምኦን ደረጄ