መደበኛ ያልሆነ

ጥቅምት 4፤2013-የብስራት ማለዳ አጫጭር ዓለም አቀፍ መረጃዎች

~ በአፍጋኒስታን ሂልማንድ ግዛት በፀጥታ ሃይሎች እና በታሊባን መካከል በተፈጠረ ውጊያ ከ 35 ሺ ያላነሱ ሰዎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው መሰደዳቸው ተሰማ፡፡

~ በአዘርባጃን አርሜንያ በናጎርኖ ካራባክ ግዛት በቀጠለው ግጭት የተነሳ ከፍተኛ የሰብዓዊ ቀውስ እየተፈጠረ ይገኛል፡፡

~ ሩዋንዳ ለአደንዣዥ እጽ ጥቅም ላይ የሚውለውን ካናቢስ ለህክምና ተግባር እንዲውል ፍቃድ መስጠቷ ተሰማ፡፡

~ የሞዛምቢክ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር አርሚንዶ ቲያጎ በኮሮና ቫይረስ መጠቃታቸው ተሰማ፡፡ ሚኒስትሩ በመኖሪያ ቤታቸው ራሳቸውን አግለዋል፡፡

~ የአሜሪካ የፌደራል የምርመራ ቢሮ /FBI/ በቤሩት በወርሃ ነሀሴ ካጋጠመው ፍንዳታ ጋር በተያያዘ በመነሻው ዙሪያ ድምዳሜ ላይ መድረስ አለመቻሉን አሣወቀ፡፡ በቤሩት ፍንዳታ 200 የሚጠጉ ሰዎች ህይወታቸውን ማጣታቸው ይታወሳል፡፡

~ በሜክሲኮ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የተነሳ የሟቾች ቁጥር ከ 84ሺ መብለጡን የjoን ሆፕኪንስ ዩኒቨርሲቲ ይፋ አደረጉ፡፡

~ የሰሜን ኮሪያ መሪ ኪም ጆንግ አን በጎርፍ አደጋ የተነሳ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ስፍራ እንዲያገግም በቀጣዮቹ 5 ዓመታት 25 ሺ መኖሪያ ቤቶች መገንባታቸው ተሰማ፡፡

በስምኦን ደረጄ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *