
በትላንትናው እለት በኮፐንሃገን በተካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጲያዊቷ ፀሀይ ገመቹ በ1፡05፡08 በማጠናቀቅ በሲፋን ሀሰን የተያዘውን ሪከርድ ሰብራለች።የ22 ዓመቷ ፀሀይ ገመቹ ሪከርዱን በሰባት ሰከንዶች ማሻሻል ችላለች።
ሀዊ ፈይሳ ውድድሩን በሁለተኛነት ስታጠናቅቅ ኬንያዊቷ ቪቪያን ኪፕላጋት ሶስተኛ ደረጃ አግኝታለች።በወንዶቹ ከፍተኛ ትንቅንቅ ከኬንያ አትሌት ጋር ያደረገው አምደወርቅ ዋለልኝ ውድድሩን አሸንፏል።
በስምኦን ደረጄ