መደበኛ ያልሆነ

መስከረም 20፤2014-በግጭት ምክንያት ተፈናቅለው ኮምቦልቻ ላይ ከሰፈሩ 320 ተፈናቃዮች ውስጥ 8 የሚሆኑ ነብሰ ጡር እናቶች በመጠለያ ጣቢያ ውስጥ መውለዳቸው ተነገረ!

ከሰሜን ወሎ ሀራ ወረዳ ተፈናቅለው በኮምቦልቻ የሰፈሩ ተፈናቃዮች ቁጥር 321 መድረሱ ተነግሯል ።

ከተፈናቃዮቹ ውስጥ 8 የሚሆኑት እናቶች በመጠለያ ጣቢያ ውስጥ የወለዱ ሲሆን በአሁን ሰራት 6 ለመውለድ የደረሱ እናቶች ናቸው ብስራት ሬድዮ በስፍራው ተገኝቶ እንደተመለከተው ከእነዚህ እናቶች በተጨማሪ 41 የሚሆኑት የሚያጠቡ እናቶች ናቸው ።

የተፈናቃዮች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እንደሚገኝም ተናግሯል ።ተፈናቃዮቹ ከሁለት ወር በላይ በመጠለያ ውስጥ አስቆጥረዋል ።

የቢጂ አይ ኢትዮጲይ ኮምቦልቻ ፋብሪካ እነዚህኑ ፣በኮምቦልቻ ፣ ደሴ ከተማዋ እና ዙሪያዋ ለሰፈሩ ከመኖሪያ ቀዬአቸው ለተፈናቀሉ ዜጎች ድጋፍ አድርጓል።

ናትናኤል ሀብታሙ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *