
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በክልልነት የመደራጀት ህዝበ ውሳኔ ድምፅ መስጠት በቦንጋ ከተማ በይፋ ተጀምሯል።በርካታ የከተማዋ ነዋሪዎች የምርጫ ካርድ በወሰዱባቸው ምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው ድምፅ እየሰጡ ይገኛሉ።
እንደ ኢዜአ ዘገባ ድምፅ የመስጠት ሂደቱም ሰላማዊ እና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድይገኛል።
የካፋ፣ ሸካ፣ ቤንች-ሸኮ፣ ዳውሮ፣ ምዕራብ ኦሞ ዞኖች እና ኮንታ ልዩ ወረዳ “በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል” ለመደራጀት የሚያካሂዱት ህዝበ ውሳኔ ሲሆን ከ 1 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ድምፅ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።