
ኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲን አስጠነቀቀች
የአሜሪካ ኤምባሲና ድርጅቶች በሀሰት መረጃዎችን በማሰራጨት መቀጠላቸውን የኢትዮጵያ መንግስት አስታውቋል።
የኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥቷል::
የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ከዚህ ቀደም አዲስ አበባ ተከባለች የሚል መረጃን ያሰራጩ እንደነበር አውስተው አሁን ደግሞ ሽብር ይፈፀማል የሚል ሀሰት መቀጠሉን አስታውቀዋል።
በመሆኑም ኤምባሲውና የአሜሪካ መንግስት የሀሰት መረጃዎችን ከማስተላለፍ እንዲቆጠቡ መንግስት አሳስቧል።