መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 27፤2014-ህወሓት በአማራ ክልል በስድስት የሀይማኖት ተቋማት ላይ ውድመት ማድረሱን መንግስት አስታወቀ

አሸባሪዉ ህወሓት በአማራ ክልል የላሊበላ ዉቅር አብያተ ክርሲቲያን የሚገኝበት ስፍራን ጨምሮ በስድስት የሀይማኖት ተቋማት ላይ ዉድመት ማድረሱን የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ድኤታ ሰላማዊት ካሳ ተናግረዋል ።

ህወሓት በወረራ ይዟቸዉ በቆዩ ቦታዎች በአንጾኪያ እና በጋሸና ንጹሀን ዜጎችን በጅምላ መጨፍጨፉን እና በአፋር እና በአማራ ክልሎች የዘር ማጥፋት ወንጀል እንደፈጸመ ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪም በ አማራ ክልል በደቡብ ጎንደር ዞን ህወሓት ወድቶችን ማስከተሉን ሚኒስትር ድኤታዋ በመግለጫቸዉ አስታውቀዋል። በዚህም እስካሁን በተደረገው ጥናት ሁለት የባህልና ቱሪዝም ተቋማት እና 22 የቱሪዝም አገልግሎት መስጫ ተቋማት ላይ ጉዳት ማድረሱን ተናግረዋል ። አያይዘውም አሸባሪዉ ህወሓት በሰሜን ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ ሊገኝ የሚችለዉን 7.1ሚሊዮን ብር ገቢ ማሳጣቱን ሚኒስትር ድኤታ ሰላማዊት በሰጡት መግለጫ ላይ አንስተዋል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *