መደበኛ ያልሆነ

ጥር 18፤2014-የቡርኪናፋሶን የመንግስት ግልበጣ የመሩት ማናቸው?

~ የቡርኪናፋሶ የመንግስት ግልበጣ የመሩት ፓውል ሄንሪ ሳንዳኦጎ ዳሚባ የሚባሉ ሲሆን በሀገሪቱ በሚደረገው የታጣቂዎችን ውጊያ በማክሸፍ ግንባር ቀደም ነበሩ።

~ የ41 ዓመቱ የመንግስት ግልበጣ መሪ ከዚህ ቀደም መፅሃፍ ፅፈው የነበረ ሲሆን ርዕሱም የምዕራብ አፍሪካ ጦር ሰራዊት እና ሽብርተኝነት እርግጠኛ ያልሆኑ ምላሾች የሚል ነበር።

~ በፈረንሳይ ወታደራዊ አካዳሚ በወንጀል ሳይንስ የሁለተኛ ዲግሪ ተቀብለዋል።

~ በ2015 የተካሄደውን መፈንቅለ መንግስት በፅኑ የተቹ ቢሆንም ከሰባት ዓመት በኃላ ራሳቸው የመንግስት ግልበጣ ፈፅመዋል።

~ ስራቸውን የጀመሩት የፕሬዝዳንቱ የግል አጃቢ በመሆን ነበር።

ባለፉት 18 ወራት በአፍሪካ ስድስት ጊዜ ያህል የመንግስት ግልበጣ ተፈፅሟል።ሁለት ጊዜ በማሊ፣ጊኒ፣ቻድ፣ሱዳን እና በቡርኪናፋሶ ተፈፅሟል።

በስምኦን ደረጄ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *