መደበኛ ያልሆነ

መስከረም 22፤2016-የ 4 ዓመት ዶሞዝ ሳይከፈላት በባህሬን የቆየችዉ ኢትዮጵያዊት ደሞዟን እንድታገኝ ተደረገ

አዲስ በየነ የተሰኘች ኢትዮጵያዊት ትሰራበት ከነበረችበት ቤት የ4 ዓመት ዶሞዝ ሳይከፈላት እንደቆየ በባህሬን ለሚገኘዉ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ሪፖርት ማድረጓን ቆንስላዉ ገልጿል።

ይህንን ተከትሎም ጽ/ቤቱ ከባህሬን የሚመለከታቸው መስሪያ ቤቶች ጋር በመነጋገር ሙሉ ደሞዟ እንዲከፈላት ማድረጉን አሳዉቋል።

ግለሰቧም ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ በዝግጅት ላይ ትገኛለች መባሉን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን በባህሬን ከሚገኘዉ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ያገኘዉ መረጃ ያመላክታል።

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *