መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 11፤2016 – ሕብረት ባንክ የሃብት መጠኑን 83 ቢሊዮን ብር መድረሱን አስታወቀ

???? ባንኩ የምስረታውን 25ኛ ዓመት ማክበር ጀምሯል

ሕብረት ባንክ የ25ተኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ ክብረ በዓሉን በይፋ በዛሬው ዕለት ያበሰረ ሲሆን በየዓመቱ ከ25 እስከ 30 በመቶ እድገት እያስመዘገበ  መምጣቱን ባንኩ አስታውቋል ።

ባንክ ባለፉት 25 ዓመታት የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ እንደዘለቀ የተገለፀ ሲሆን ከ15 ዓመታት በፊት ሞባይል ባንኪንግን ኤስኤምኤስ ባንኪንግ በሚል በመጀመር ቀዳሚ ባንክ እንደሆነ የባንኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ አ/ቶ መላኩ ከበደ መናገራቸውን ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ሰምቷል ።

በተጨማሪ ባንኩ የኮር ባንኪንግ ሲስተም ከውጭ ሀገር ዜጎች ውጭ በራሱ ሰራተኞች መተግበሪያ በማበልፀግ በኢትዮጵያ ብቸኛው ባንክ መሆኑንን አ/ቶ መላኩ ተናግረዋል ።

ሕብረት ባንክ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ ካፒታሉ 9 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ፣ 60 ቢሊዮን ብር ብድር ፣ 64 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ተቀማጭ ያለው ሲሆን የሃብት መጠኑ 83 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተነግሯል ። የ25ተኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ ክብረ በዓሉን ዓመቱን በሙሉ በተለያዩ ሁነቶች እንደሚያከብርም ተጠቁሟል ።

በአበረ ስሜነህ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *