መደበኛ ያልሆነ

ህዳር 11፤2016 – የኦሞ ወንዝ ባስከተለዉ ጎርፍ በ21 ደሴቶች የሚኖሩ አርብቶ አደሮች በውሃ ሙላት ተከበዋል

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የኦሞ ወንዝ ከመጠን በላይ ሞልቶ  በመፍሰሱ በዳሰነች ወረዳ ከሚገኙ 40 ቀበሊያት ዉስጥ 34 ቀበሌዎችን ማጥለቅለቁ ተነግሯል ።

ወንዙ 79,828 የቤተሰብ አባላትን ያፈናቀለ ሲሆን ቀደም ሲል ከ62 ሺህ በላይ ሰዎችን አፈናቅሎ ቆይቶ በቅርቡ ደግሞ ከ17 ሺህ በላይ ሰዎችን ማፈናቀሉ ተገልጿል ።

በተፈጠረው የውሃ መጥለቅለቅ በተቋማት ላይ ከፍተኛ አደጋ ያስከተለ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 2 ጤና ጣቢያ፣ 17 ትምህርት ቤቶች እና ሌሎችም ተቋማት ሙሉ በሙሉ በውሃ ተሸፍኗል። በተጨማሪም 123 ሺህ ሄክታር የእንስሳት የግጦሽ መሬት ሙሉ በሙሉ በውሃ መሸፈኑ ተጠቁሟል ።

በአሁኑ ወቅት በወረዳዉ የሚገኙ 21 ደሴቶች ዉስጥ የሚኖሩ የቤተሰብ አባላትና ከአንድ ሚሊዮን በላይ እንስሳቶች በውሃ ሙላት ሲከበቡ ከነዚህም ዉስጥ ከ89 ሺህ በላይ ከብቶች ብቻ ማዉጣት መቻሉን የዳሰነች ወረዳ አስተዳዳሪ አ/ቶ ፍቅረማሪያም አይመላ ከብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል ።

ወረዳው ከፌዴራል አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ጋር ወይይት ማድረጉ የተገለፀ ሲሆን አንድ ጀልባ ወደ ወረዳው መግባቱ ተገልጿል ። በአደጋው ለተፈናቀሉ ወገኖች መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ድጋፍ ያደረጉ ቢሆንም ከጉዳቱ አንፃር ተጨማሪ ድጋፍ የሚያስፈልግ በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በመተባበርና በመቀናጀት አፋጣኝ ምላሽ ሊሰጡ እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል ።

በአበረ ስሜነህ

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *