
የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እና የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ትናንት ሀሙስ በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በዩክሬን ግጭት ዙሪያ ተወያይተዋል።የዩክሬን ጦርነትን በተመለከተ የኤርትራው ፕሬዝዳንት “አለም አቀፍ የዋልታ የመሆን ስርዓትን ለመፍጠር የነበረው ቅዠት ሙሉ በሙሉ ከሽፏል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ዓለምን ለአደጋ ያጋለጠውን የቅኝ ግዛት እና የግዛት ታሪክን ለመቋቋም እና ለመዋጋት የተቀናጀ ጥረት እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል ።የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር የማነ ገብረመስቀል ውይይቱ “በዩክሬን ስላለው ጦርነት ተለዋዋጭነት” እና የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ማጠናከር ላይ ነበረ ሲሉ ተናግረዋል።
“ውይይቶቹ በዩክሬን ያለውን ጦርነት ተለዋዋጭነት እና በሃይል፣ በማዕድን ማውጫ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በትምህርት እና በጤና ዘርፎች ላይ ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ማሳደግ ላይ ያተኮረ ነበር” ሲሉ የማነ በትዊተር ገጻቸዉ ላይ አስፍረዋል።እ.ኤ.አ በመጋቢት 2022 የሞስኮ ዩክሬን ጦርነት ተከትሎ ሩሲያን ለማውገዝ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውሳኔ በመቃወም ድምጽ የሰጠች ብቸኛዋ አፍሪካዊት ሀገር ኤርትራ መሆኗ ይታወሳል።
ላቭሮቭ ኤርትራ የገቡት በስድስት ወራት ውስጥ ባደረጉት ሁለተኛ የአፍሪካ ጉብኝታቸው የመጨረሻ ዙር ሲሆን ወደ አንጎላ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ኢስዋቲኒ አቅንተዋል፡፡
በስምኦን ደረጄ