👉 የሰባት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ሙሉ በሙሉ አልፈዋል
የ2014 ትምህርት ዘመን የ 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውጤት ሪፖርት ዋና ዋና ግኝቶችን በተመለከተ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ማብራሪያን ሰጥተዋል።የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑን ተከትሎ ማብራሪያን በሰጡበትም ወቅት ይህ የፈተና አሰጣጥ ሂደት ለመጀመሪ ጊዜ መሆኑን በማንሳት ፈተና ተማሪዎችን በትክክል እየመዘኑ ባለመሆኑ የጨለማ ጉዞ መቆም አለበት የሚለው እሳቤን ተከትሎ የተሰራ መሆኑን መናገራቸውን ብስራት ሬዲዮ ከፕሮፌሰር ብርሃኑ ሰምቷል።
የዘንደሮው የፈተና ጊዜ ከአንዳንድ እክሎች በስተቀር በሰላም የተጠናቀቀ በመሆኑም የጸጥታ አካላት የክልል ትምህርት ቢሮ፣ የክልል መንግስታት እንዲሁም ሌሎች አካላትን ያመሰገኑ ሚኒስትሩ የዘንድሮው ፈተና ለመጀመሪያ ግዜ ያለምንም አይነት ስርቆት እና የፈተና እክል የተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል።በፈተና ወቅት በነበሩ የደንብ ጥሰቶች 20ሺህ 170 ተማሪዎች ተቀጥተዋል ያሉት ሚኒስትሩ ይህ በመሆኑ 896ሺህ 520 ተማሪዎች ብቻ ፈተናውን መጨረሳቸውን ገልፀዋል።
በሀገር ደረጃ የተመዘገበ ከፍተኛ ውጤት ከሰባት መቶ 666 (በተፈጥሮ ሳይንስ ) ሲሆን በማህበራዊ ሳይንስ ከስድስት መቶ 524 ተመዝግቧል።ወንዶች ከሴቶች የተሻለ በውጤት ልዩነት ያመጡ ሲሆን እንዲሁም በአዲስ አበባ፥ ሀረሪ እና ድሬዳዋ የተሻለ ነጥብ የተመዘገበ ሲሆን በሌሎች ክልሎች የተለየ መበላለጥ አለመኖቱን አክለዋል።
በጠቅላላው በአማካይ ከ 50 በመቶ በላይ ያመጡት ከተፈጥሮ ሳይንስ 22 ሺህ ተማሪዎች ፣ ከማህበራዊ ሳይንስ 6973 ተማሪዎች ብቻ አልፈዋል።እንዲሁም 7 ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች በሙሉ ማሳለፋቸውን ፕሮፌሰር ብርሃኒ ነጋ ጠቁመዋል ።
በስተመጨረሻም ከ 29 ሺህ 900 ተማሪዎች ውጭ የቀሩት ተማሪዎችን ይሆናሉ ለሚለውም ጥያቄ ከ 50 በመቶ በታች ያመጣ ማንም ተማሪ በሚቀጥለው አመት ፍሬሽ ማን ሆኖ ዩኒቨርሲት እንደማይቀላቀል አስረድተዋል ላ።
በቀጣይ በቀረበው የመፍትሄ አቅጣጫ ከ59 በመቶ በታች ያመጡ ተማሪዎች በዩንቨርሲቲ ዳግም እንዲማሩ ተደርጎ በአመቱ መጨረሻ እንዲፈተኑ ይደረጋል።
ሚኒስትሩ ጨምረው የወደቁት ተማሪዎቻችን ብቻ ሳይሆኑ የወደቅነው እንደሃገር ነው ያሉ ሲሆን ተማሪዎች በሚገባው ስነ ምግባር ትምህርታቸውን አለመከታተላቸው ሁሉም ተጠያቂ ነው እንዲሁም በመንጋ ደረጃ እንደፖለቲካ አስቦ እዚህ ደረጃ ላይ መድረሳችን ያሳዝናል ሲሉ ጨምረው ተናግረዋል።
ቤተልሄም እሸቱ