በአሜሪካ መዲና ክስተቱ ከተፈፀመ ዉሎ አድሮአል።።።በአጋጣሚም ከክስተቱ ከጥቂት ቀናት በኃላ ከቤተሰብ ጋራ የስፖርቱን በአል ለመታደም ወደመዲናዋ አቀናን።።።ካለፍንበት አይቀር በማለት ቤተሰብን ይዤ ነጭ ቤት ተብሎ በሚጠራዉ ወደ አሜሪካ ቤተመንግስት ደጃፍ አቅንተን ነበር።።።።ይህቺን የነፃነት እና የብሩህ ተስፋ የተጎናፀፈችን አገረ አሜሪካን ከተቀላቀልኩ አመታቶች ሳስቆጥር በዚህ በቤተመንግስት ደጃፍ እግሬን ሳስረግጥ ይህ የመጀመሪያዬ ባይሆንም ባሁኑ ግን ውስጤ ነጩ ቤት ክብር የሌለዉ ወና ባዶ ቤት መስሎ ታየኝ።።።።።ጥቁር ስለሆነ ብቻ ሳይሆን ከዛም አልፎ ባባቱ ከጎረቤት አገር ኬንያዊ: በናቱ ነጭነትን ይዞ በሃይማኖት አባቱ ሙስሌም ሆኖ: የናቱን ሃይማኖት ክርስትናን መርጦ በዉነት ይህቺን ብኩን አለምን የመሰለ የአሜሪካ ፕሬዘዳንትን የዛሬ ሰባት አመት ገደማ ስንመርጥ በኩራት እና በደስታ ነበር።።።።የነጩን ቤት ስልጣን ከተረከበ በኃላም በአሜሪካ የፖለቲካ ታሪክ ይከናወናሉ ተብለዉ ያልታሰቡትን አጀንዳዎች በከባድ ሰላማዊ ጦርነት እዉን እንዲሆኑ በማድረጉ እጅ ነስተናል።።።ሆኖም ከቀናቶች በፊት ግን የአሜሪካ ሱፕሪም ኮርት በ ግብረሰዶማውያን ላይ በወሰኑት አሳዛኝ ዉሳኔን አስታኮ ከሁለት መቶ አመት በላይ ተከብሮ በርካታ ፕሬዘዳንቶችን አሳልፎ እዚህ የደረሰዉን ቤተመንግስት እንዲረክስ አድርጎታል።።።።በግሌ ከአምላክ ትእዛዝ ዉጪ መመራትን ባልቀበለዉም።።።።የፕሬዘዳንቱ ዉሳኔ እራሱን የቻለ ሌላ ፖለቲካዊ ትርምስ እንዳለዉ ይገባኛል።።።።ነገር ግን ንብረቱ የአሜሪካ ህዝብ የሆነዉን ቤተመንግስት።።።ፕሬዘዳቶች እንዲሰሩበት እና እንዲኖሩበት ይሰጣቸዋል እንጂ በቤተመንግስቱ ላይ ደስታን ለመግለፅ በቁጥር ከሶስት ፐርሰንት ለማይበልጡት የግብረሰዶማውያንን ምልክት የሆነዉን ቀለም ማብራት በከፍተኛ ደረጃ ህዝብን መናቅ እና መድፈር ነዉ።።።።። ፕሬዘዳንት ኦባማ ለዚህም ነዉ ማኔ ቴቄል ፋሬስ ያልኮት።።።አዎ በጣም ቀለዉ ተገኝተዋል።።።።ይህን ቅለት ይዘዉ በቅድስት ኢትዮጲያ ለመሄድ ዝግጅት ላይ እንደሆኑ ይታወቃል ይህን ትርምሶን አገሪቷ አትፈልገዉም።
የሚጠቅማትን ይዘዉ ይሂዱ።
ማኔ ቴቀል ፋሬስ (ተመዝነህ ቀለህ ተገኘህ)
ዘካርያስ ጌታቸዉ