ጦማር/ዜና

የኦባማ ስኬት/የአፍሪቃ ጉዞ

የአሜሪካ ፓለቲካ ሂደት እጅግ ከባድ እና ዉጣ ወረድ ያለዉ ነዉ። ፖለቲካዉ በሁለት ትላልቅ ፓርቲዎች የተወጠረና ፓርቲዉን የሚመሩት ግለሰቦች ከአገራዊ አመለካከት ለፓርቲአቸዉ አድልኦ ስላላቸዉ አንድ ፕሬዘዳንት የሚፈልገዉን ሰርቶ መቀመጫዉን ለመልቀቅ በጣም አስቸጋሪ ነዉ። ፕሬዘዳንት ኦባማ ከብዙ መሰናክሎች በኃላ የሚከተሉትን በታሪክ እንዲዘገቡ አድርገዋል።
1, የቀጥታ 65 ወራቶች የኢኮኖሚ እድገት
2, የግል ስራዎች እድገት ( longest period of private sector job creation in American history)
3, ስርአጥነት ከ10.1(2009) ወደ 5.4 መዉረድ(2015)
4, ፕሬዘዳንቱ ቢሮዉን ከተረከቡ ጀምሮ የካንፓኒዎች አክስዮን እድገቱ በሬኮርድ ነዉ።( The stock market continues to set new record high)
5, የመንግስት ብሔራዊ እዳ በ2/3 መዉረድ (ከ2009 በኃላ)
6, በፕሬዘዳንቱ ጃንጥላ ስር የመንግስት ወጪ ያደገዉ በ3.3% ብቻ ነዉ። ይህ ከቀድሞዉ ፕሬዘዳንት አይዘንሃወር በኃላ የመጀመሪያዉ ነዉ።
7, የቀረጥ ክፍያ ለ95% የአሜሪካ ከፋዮች አንሶአል። ይህ በ50 አመት ታሪክ ዉስጥ የመጀመሪያዉ ነዉ
8, ኦባማ ኬር(Affordable Care Act) በሚባለዉ አማካኝነት ወደ 10ሚሊዮን የሚሆኑ ግለሰቦች የህክምና ኢንሹራስ አላቸዉ
9, በ11 አመት ታሪክ ዉስጥ አሁን በቁጥራቸዉ የሚያንሱ ወታደሮች፣ አየር ሃይሎች፣ ማሪኖች በጦርነት ቦታ ላይ ይገኛሉ
10, በፕሬዘዳንቱ ዘመን: ከምንም ጊዜ በበለጠ ወረቀት የሌላቸዉ ዜጎች ተይዘዋል: ወደመጡበት እንዲመለሱም ተደርገዋል።
11, በምንም መልኩ ሊታሰብ የማይችለዉን ኒዉክለርን በተመለከተ ከኢራን ጋራ ሰላም እንዲወርድ አድርገዋል።

ፕሬዘዳንቱ አንድ አመት ከጥቂት ወራቶች ይቀራቸዋል። አንዱ የሚቀጥለዉ አጀንዳቸዉ የአለምን አዳጋች የአየር ንብረትን በተመለከተ ይመስላል። ወደ አሁግረ አፍሪቃ አንቅተዉ ዛሬ ያባታቸዉን አገር ኬንያን ለመጎብኘት እና እናት ኢትዮጰያን ለማየት ምድረ አፍሪቃን ይረግጣሉ…እሮብ ለት በቤተመንግስታቸዉ የ(African Growth and Opportunity Act) ሲፈርሙ አፍሪቃ የሚቀጥለዉ የአለም የኢኮኖሚ ምሰሶ እንደምትሆን ተናግረዋል….ባለፈዉ ወር ፕሬዘዳንቱ ከሀጉሪቷ ጋራ ያለዉን የTrade authority ለ10 አመት ያስቀጠሉት ሲሆን… ይህ ትሬድ ወደ 350000 የሚሆኑ ስራዎችን እንደሚያቅፍ ተነግሮአል….ኢትዮጰያ ምንም እንኳን በቀድሞዉ ንጉስ በግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ዘመን ከአሜሪካ መሪዎች ጋራ የነበራት ትስስር ጥሩ ቢሆንም መሬቷን ለመርገጥ የደፈረ እና የታደለ ፕሬዘዳንት ማንም አልነበረም…ይህ የፕሬዘዳንት ኦባማ ጉብኝት በኢትዮጰያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ይሆናል።

ቸር ይግጠመን

ጦማር/ዜና

ቀዳማዊ ኃይለስላሴ

ቀዳማዊ ኃይለስላሴ በዲፕሎማሲያዊ ክህኖታቸዉ እና ከምእራብ አገሮች መሪዎች ጋራ በነበራቸዉ ቅርበት: የአሜሪካ ፕሬዘዳቶች በአፍሪካ መዲና በአገረ ኢትዮጰያ ብቅ ትልቅ ቢሉ ምንም አያስገርምም ነበር,
ይህ ሊሆን አልቻለም። እግዚአብሔር የፈቀደዉ አህጉሯን የመሰለ, በመምሰል ብቻ ሳይሆን በደሙ አፍሪካዊ በዜግነት አሜሪካዊ የሆነ ፕሬዘዳንት በምስራቅ አፍሪቃ በታላቋ የታሪክ ባለቤት ኢትዮጰያ እና በጎረቤት እና ለፕሬዘዳንቱ ከፊል ባለቤት በሆነቺዉ ኬንያ እንዲመጡ ሆነ።

በዚህ ታሪካዊ ጉብኝት ይህንን ለማለት ወደድን
ያባታቸዉን አገር እንደረገጡ ያስቀደሙት በግራ እህታቸዉን በቀኝ አያታቸዉን አስቀምጠዉ ከዘመዳዝማድ ጋራ እንጀራ መቁረስን የመረጡበት ምሽት አይረሴ ነበር
በስታዲዮሙ ያደረጉት ታሪካዊ ንግግራቸዉ እና ሌሎችም ክንዋኔዎች ቢኖሩም በጋዜጠኞች ስብሰባ ላይ ያገሩ ፕሬዘዳንት ኬንያታ ግብረሶዶማዉያንን በተመለከተ, “ይህ የናንተ ችግር ነዉ የአፍሪቃ አይደለም ብዙ ሊፈወሱ የሚፈለጉ ችግሮች አሉን ለዚህ ቦታ አንሰጠዉም” ያሉት, አገራቸዉን ብቻ ሳይሆን መላዉ አፍሪካን ያኮራ መልስ ነበርና እጅ ነስተናል

አዲስ አበባ ህዝቧ ብቻ ሳይሆን የነበረዉ በአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ምክንያት አፍሪካዉያን ከነመሪዎቻቸዉ በመዲናችን ነበሩና ይህንን ጉብኝት ታሪካዊ እና ግለት እንዲኖረዉ አድርጎታል

በታላቁ ቤተመንግስት የእራት ግብዣ ላይ የሰዉን መጀመሪያነት በኢትዮጰያ ያረጋገጠችልንን ከእናት ሉሲ ጋራ መገናኘታቸዉ እና ትከሻቸዉን በስክስታ ወዝወዝ ያደረጉበት እና የቡናና የእጣኑ ምሽት ኢትዮጰያዊነትን አላብሶአቸዉ ነበር ።

በአፍሪካ ህብረት ታሪክ, ተቀማጭ የአሜሪካ መሪ ብቻ ሳይሆን, አለም ያላሰበችዉ የአሜሪካ ጥቁር ፕሬዘዳንት ከወድሞቻቸዉና ከእህቶቻቸዉ ጋራ በአባት ኔልሰን ማንዴላ ስም በተሰየመ አዳራሽ ጣሪያ ስር የታሪካዊ ንግግር ክስተት, መቼ ሊደገም ይችላል የሚለዉን ጥያቄ እንዳናስበዉ ያደርገናል።

በንግግራቸዉ ላይ ለሰዉ ልጅ እኩልነት, መብት እንዲሁም ክብር የሰጠው ትምህርታዊ መልእክት ለታሪክ የሚቀመጥ ነዉ። ከምንም በላይ ግን የስልጣን ዘመንን በተመለከተ ምነዉ ወድሞቼ ይህ አላስፈላጊ እና ሊገባኝ እማይችል ጉዳይ ነዉ, በተለይ ባለሃብት ሆናችሁ ማረፍን አለመፈለጋችሁ የሚገርም ነዉና እባካችሁ ስላጣንን ዉስን አድርጉት ያሉት ንግግር ከጆሮ እማይወጣ ነዉ።

ለአሜሪካ ቀረጥ ከፋዮች ወደ ስድስት ሚሊዮን ዶላር ያወጣዉ ይህ የሁለቱ ጎረቤታማቾች ጉብኝትን ሁለቱም አገሮች በሰላም ስለተወጡት ሊመሰገኑ ይገባል።

በመጨረሻ አንድ ነገር ልበል, በፈረንጆች አቆጣጠር በ1973 የኩባዉ መሪ “በኛ እና በአሜሪካ ሰላም ሊወርድ የሚችለዉ አሜሪካ ወደፊት ጥቁር ፕሬዘዳንት ሲኖራትና የካቶሊክ ፖፕ ከላቲን አሜሪካ ሲመረጥ ነዉ” ብለዉ ነበር። ይህንን ትንቢት ትላንት የአፍሪካዉ ህብረት ዋና ሃላፊ ዶክተር ዙማ ፕሬዘዳንት ኦባማን ሲያስተዋዉቁ አንስተዉት ነበር። የሚገርም ክስተት።

ቸር ይግጠመን!

ጦማር/ዜና

የአቤል የመድረክ

ማቀንቀን ከጀመረ አምስት አመታትን አሳልፏል, ስሙም በመላዉ አለም በአጭር ጊዜ ዉስጥ ነዉ እንደእንዝርት መዞር የጀመረዉ,,,በአጭር ጊዜ ዉስጥ በሙዚቃ አለም እንዲህ አይነት ስኬትን ያዘለችን ምድርም እንኳን ግራ ሳይገባት አይቀርም። አዎ እማወራዉ ምንም እንኳን እትብቱ በእናት ኢትዮጰያ ባይቆረጥም: በናቱም ባባቱም ኢትዮጰያዊ ደም ያለዉን: በኛ ዘንድ ብዙም ያልተወራለትን አለም ግን እጅ እየነሳችለት ስላለዉ ድምፃዊ፣ ዘፈን ፀሃፊ እና የሬኮርድ ፕሮዲዉሰር ’አቤል ተስፋዬ ’አካ ዊኬንድ’(The Weeknd)ነዉ።

በአንዳዶቹ የሚቀጥለዉ ማይክል ጃክሰን የሚሉት ይህ ታሪካዊ ወጣት ድምፃዊ የተወለደዉ በፈረንጆቹ ካላንደር በ1990 ላይ በጥቅምት ወር ላይ ሲሆን: ቦታዉም በካናዳ በስካርብሮ በኦንትርያል ነዉ። እናትና አባቱ ከኢትዮጰያ የወጡት በፈረንጆቹ ካላንደር በ1980ዎቹ ላይ ነበር። አቤል ሲያድግ አባቱ አብሮት ስላልነበረ እናቱ ደሞ በጣም በስራ የተወጠረች ስለነበረች አቤልን ያሳደጉት አያቱ ስለነበሩ አቤል አፉን የፈታው በአማርኛ ስለነበረ አማርኛ በደንብ ያወራል።

የአቤል የመድረክ ስም ዊኬንድ የሚባል ሲሆን የዚህ ስም አመጣጥ አቤል በ17 አመቱ ላይ ከሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በቃኝ ብሎ ከትምህርት ሲሰናበት: በዛዉ ነበር ቤቱን በሰንበት(Weekend) ላይ ለቆ ያልተመለሰዉ። በዚህም ምክንያት ነዉ የመድረክ ስሙን ዊኬንድ(Weeknd) ያለዉ። አፃፃፉን ለየት ያደረገዉ በካናዳ አገር ተመሳሳይ ስም ያላቸዉ ባንድ ስለነበረ የሱን በአንዲት ፊደል እንድትለይ ሆነ።

በፈረንጆቹ 2010–11 ላይ ነበር በቶሮንቶ ከተማ ጀርሚ ሮስ የተባለዉን ፕሮዲዉሰር አግኝቶ ወደ መጀመሪያዉ አልበሙ የገባዉ። አቤል በዚህ የፍጥነት ጎዳናዉ ላይ ስለነበረዉ ግስጋሴ ብዙ ማለት እችል ነበር አሁን ግን ቀጥታ በዚህ በአጭር የስኬት ጉዞ በእጁ የጨበጠዉን አንዳንድ ሽልማቶችን ለማየት እንሞክር።

በ2012 የዌብ ቦርን(Web born Artist)፣ ብሬኪንግ ዉዲ(Breaking Woodie)፣ የአመቱ ሶሎ አርቲስት(Sol Artist os the year)፣ የብሬክትሩ(Breakthrough) እና የአር ኤንድ ቢ(R&B) ምርጥ ቅጂ በመሆን የተሸለመ ሲሆን

በ2013 በምርጥ ቪዲዮ፣ ምርጥ አዲስ ዘፋኝ እንዲሁም በሌሎች እጩ ነበር
በ2014 የአላን ስላይት(Allan Slaight) ተሸላሚ እና የአመቱ ምርጥ አርቲስት ሆኗል

በ2015 የሴንትሪክ አዋርድ(Centric) ተሸላሚ ሲሆን አመቱ ስላላለቀ በተለያዩ አዋርዶች እጩ እንደሆነ ለማየት ችለናል።

የአቤል ትልቁ ስኬት አንድ ዘፋኝ ዘፈኖቹ በሙዚቃ ቢል ቦርድ በአንድ ጊዜ አንደኛ፣ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ሲሆን በአለም የዘፋኝ ታሪክ ይህ ለመጀመሪያ ነዉ። ማንም ዘፋኝ ከነማይክል ጃክሰን ጀምሮ ይህ ዉጤት የለዉም። The Hills, Earned it, ‘Can’t Fell My Face የተባሉት ዘፎኖቹ ከአንድ እስከሶስት ቢል ቦርድን (Billboard) ተቆጣጥረዉት የነበረዉ። አሁንም በዚህን ሰአት በቢል ቦርድ ላይ ቁጥር አንድ ዘፈን
‘Can’t Fell My Face የተባለዉ የኢትዮጰያዊው አቀንቃን የአቤል ተስፋዬ አካ ዊኬንድ(The Weeknd) ነዉ።

ጋብዣለሁ

ጦማር/ዜና

ለኬንያ እጅ ነስተናል

በቻይና የተደረገዉ የዘንድሮዉ የአለም አቀፍ የአትሌቲክስ ሻንፒዎና ውድድር ለአፍሪቃ ትልቅ ታሪክ የተሰራበት እና አፍሪቃ በተወሰነ ውድድር አለመወሰኟን ለአለም ያስመሰከረችበት ጊዜ ነበር።

ምንም እንኳን አገራችን በወንዶች ህዝቧ የጠበቀዉን ዉጤት ባታገኘም በሴቶች አስከትላ መግባቷን እና ሬኮርድ መስበሯን የቀጠለችበት ውድድር ነበር። ከሁሉም በላይ ግን ሊወራላት እና እጅ ሊነሳላት የሚገባት ጎረቤቷ ኬንያ ናት።
ኬንያ በዘንድሮ የአለም አቀፍ ውድድር ላይ አፍሪቃ በመላዉ የአትሌቲክስ ውድድርን በተለይ የትራኩን ውድድር ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር የተወሰኑ ውድድሮች ብቻ እንደቀራት ያሳየችበት ጊዜ ነበር። አፍሪቃ በርቀት ውድድር መረብ ውስጥ እራሷን ወስና ለብዙ አመት የተቀመጠችዉ የልጆቿን ሁለገብ ችሎታን ባለማወቅ ሆነ በሌሎች የውድድር ዘርፎች ልምድን እናን ስልጠናን አለማካበት ይሁን ሌላም ነገር ይህ ነዉ ለማለት ባልችልም: ዘንድሮ በአራት መቶ መሰናክል እና በጦር ውርወራ ወር ቅን በጇ ስታስገባ ለአፍሪቃኖች ለሌሎችም ለማይታሰቡ ውድድሮች በሩን ማንኳኳት እንደሚቻልና ለሌላዉ አለማት የልብ ትርታን የጨመረበት ጊዜ ነበር።

አፍሪቃ የኦሎንፒክ ድልን ለመጀመሪያ ጊዜ እንድታይ ያደረጋት በጀግኖቹ የኢትዮጰያ አትሌቶች በነበቂላ እና ማሞ ነበርና አትሌቶቿ ተሳትፎአቸዉ እና ድሎቿ በማራቶን፣ በአስር ሺህ እና በአምስት ሺህ የተወሰነ ነበር። ከዘመኖች መሸጋገር በኋላ እንሆ ዛሬ በማራቶን፣ አስር ሺህ፣ አምስት ሺህ፣ ሶስት ሺህ፣ አንድ ሺህ አምስት መቶ፣ ስምንት መቶ፣ ሶስት ሺህ እና አራት መቶ መሰናክል እንዲሁም በጦር ውርወራ የወረቅ ባለቤት ሆናለች። እንግዲህ በትራኩ የቀራት ሁለት እና የመቶ ሜትር ሩጫ እና የዱላ ቅብብል ብቻ ሲሆን ትኩረት ከተሰጠበት የመሬት እና የከፍታ ዝላዩ እንዲሁም ሌሎች ውድድሮች በአፍሪቃ ጉሮሮ ውስጥ ማለፍ እማይችሉበት ምክንያት የለም።

ዘንድሮ ለመጀመሪያ ጊዜ በአለም አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድር በሜዳልያ ጠረጴዛ አፍሪቃ በልጆቿ ኬንያ እና ኢትዮጰያ የአንድ እና የአምስተኛ ደረጃን መያዝና ኬንያ እነ አሜሪካን፣ ቻይናን፣ እንግሊዝን አስከትላ በአንደኛ ደረጃ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ተቀምጣ ማየት እጅጉን የሚያኮራ እና ለሚቀጥለዉ ትዉልድ አበረታችና ለአሁጉሯ አነቃቂ መድሃኒት ነዉ።
የኬንያን አትሌቶች ከታላቅ አክብሮት ጋራ እጅ ነስተናል።

መደበኛ ያልሆነ

ብስራት-ምስረታ

Oyaya Multimedia is a company established on the foundation laid by “Eger Kuasin Be Radio Temelketu” by Messele Mengistu which has been admired and esteemed by all Ethiopians in the past five years.

This company has now grown to a level where it can establish Bisrat FM 101.1 Radio Station which is able to win the hearts and minds of many Ethiopians within a short time of its launching.

Bisrat FM 101.1 is an infotainment station focusing on Sport, Entertainment and other latest issues. It is broadcasted live to its listeners in and around the city of Addis Ababa while listeners outside of Ethiopia can tune into the programs via our website bisratfm101.1 (live streaming) for 18 hours a day and 7 days a week from 06:00 am – 12:00 pm. We cordially invite you to cooperate with Bisrat FM 101.1 which has successfully penetrated into the hearts of Ethiopians.

Please stay tuned to Bisrat FM 101.1 from the morning dawn at 06:00 am to the darkness at 12:00 pm.